ከ«ሲንጋፖር» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
r2.7.1) (ሎሌ ማስተካከል: gd:Singeapòr
r2.5.2) (ሎሌ መጨመር: as:ছিঙ্গাপুৰ
መስመር፡ 32፦ መስመር፡ 32፦
[[ar:سنغافورة]]
[[ar:سنغافورة]]
[[arz:سينجابوره]]
[[arz:سينجابوره]]
[[as:ছিঙ্গাপুৰ]]
[[ast:Singapur]]
[[ast:Singapur]]
[[az:Sinqapur]]
[[az:Sinqapur]]

እትም በ17:22, 6 ማርች 2012

የሲንጋፖር ሥፍራ በመላይ ልሳነ ምድር ጫፍ

ሲንጋፖር ከተማ-አገር ነው።

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 3,438,600 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 01°18′ ሰሜን ኬክሮስ እና 10°50′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

ታሪክ

የግሪክ መልክዐ ምድር አዋቂ ቶሌሚ (150 ዓ.ም. ግድም) በዚያ ሥፍራ ሳባና የተባለ የንግድ ወደብ በካርታው ላይ አሳየ። በ250 ዓ.ም. ግድም ደግሞ አንድ ቻይናዊ መዝገብ በዚያው ቦታ ፑ ልዎ ቾንግ የተባለ ደሴት ይገልጻል። በ680 ዓ.ም. ገዳማ ደሴቱ በሽሪዊጃያ መንግሥት ግዛት መካከል ሆነ። ከ1300 ዓ.ም. በፊት ተማሲክ የተባለ መንደር ነበረበት። በአንድ ትውፊት ዘንድ ሳንግ ኒላ ኡታማ የሚባል የሽሪዊጃያ መስፍን ያንጊዜ ስሙ ሲንጋፑራ («የአንበሳ ከተማ») የሚባል ከተማ በተማሲክ ደሴት ላይ ሠራ።

ሲንጋፖር በሌሊት

በ1400 ዓ.ም. አካባቢ የሽሪዊጃያ መንግሥት ሲደክም ጎረቤቶቹ ማጃፓሂትሲያም ይታግሉበት ነበር። ሆኖም ሲንጋፖር ሽሪዊጃያን የተከተለው የመላካ ሡልጣንነት ማዕከል ሆነ። በ16ኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም. ላይ ይህ ሡልጣንነት ከፖርቱጋል ጋር ተጣለና በ1605 ዓ.ም. ፖርቱጊዞች ሲንጋፖርን አቃጠሉት።

የነበረው ከተማ ጠፍቶ ዙሪያው በፖርቱጊዞች ይገዛ ነበር፤ ብዙም ሳያልፍ የሆላንድ ነጋዴዎች ዙሪያውን አስተዳደሩ። የሲንጋፖር ደሴት እራሱ በይፋ በጆሖር ሡልጣን ግዛት ነበር። በ1811 ዓ.ም. የእንግሊዝ አገረ ገዥ ስታምፎርድ ራፈልዝ የሆላንድ ነጋዴዎችን ላዕላይነት ለማቃወም አስቦ ፡ የጆሖር ሡልጣን ጣውንት ወንድሙን ለሡልጣንነቱ ደግፎ ፡ በደሴቱ ላይ አዲስ ከተማ ለመመሥረት ፈቃድ በዚያ አገኙ። የብሪታንያ ቅኝ አገርና ንግድ ጣቢያ ሆኖ በቶሎ አደገ፤ በ1815 ዓ.ም. ጆሖር ደሴቱን ለእንግሊዝ መንግሥት ሸጠው። በብዛት በሲንጋፖር የሰፈሩት ሰዎች ቻይናዊ ነበሩ።

1934 እስከ 1937 ዓ.ም. በ2ኛው አለማዊ ጦርነትጃፓን ሃያላት ሲንጋፖርን በግፍ ያዙ፤ በዚህም ወቅት የከተማው ስም ሾናንቶ ተብሎ ይሉት ነበር። ከጦርነቱ በኋላ ሲንጋፖር በ1950 ዓ.ም. ራስ-ገዥ ሁኔታ ከእንግሊዝ አገኘ። በ1956 ዓ.ም. ግን በነጻ ፈቃዱ ሲንጋፖር በአዲሱ የመላይዢያ ፌዴሬሽን ውስጥ ክፍል ሆነ። ይህ ሁኔታ እስከ 1957 ዓ.ም. ብቻ ድረስ ቆየ፤ ትብብሩ ለጸጥታ ተስማሚ ስላልሆነም መላይዢያ ሲንጋፖርን ከፌዴሬሽኑ አስወጥቶ የዛኔ እስካሁን ድረስ የሲንጋፖር ሬፐብሊክ ሆነ።

ቋንቋዎች

በሲንጋፖር 4 ይፋዊ ልሳናት አሉ። እነርሱም መላይኛእንግሊዝኛቻይንኛ (ፑቶንግኋ) እና ታሚልኛ ናቸው። መላይኛ ደግሞ ብሔራዊ ቋንቋ ነው።

መለጠፊያ:Link FA