ከ«ማርሐሺ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
No edit summary
r2.7.2) (ሎሌ መጨመር: ca, es, fa, fr, gl, no, oc, ru ማስተካከል: en
መስመር፡ 10፦ መስመር፡ 10፦
[[መደብ:የእስያ ታሪክ]]
[[መደብ:የእስያ ታሪክ]]


[[en:Marhashi]]
[[ca:Warakshe]]
[[en:Marhasi]]
[[es:Marhasi]]
[[fa:پرشی]]
[[fr:Marhashi]]
[[gl:Warakshe]]
[[no:Marhashi]]
[[oc:Marhashi]]
[[ru:Мархаши]]

እትም በ17:25, 7 ዲሴምበር 2012

ማርሐሺ (ባርሐሺ፣ ዋራሕሼ) በጥንት በኤላም አጠገብ የተገኘ አገር ነበር። በአዳብ ንጉሥ ሉጋል-አኔ-ሙንዱ ግዛት ከ፯ቱ ክፍላገራት ከኤላምና ጉቲዩም መካከል በአንድ መዝገብ ይቆጠራል። ደግሞ የማርሐሺ አለቅ ሚጊር-ኤንሊል በአመጽ ተነሥቶ ሉጋል-አኔ-ሙንዱ እንደ ተወጋው ይላል።

በኋላ የአካድ ንጉሥ ታላቁ ሳርጎን ማሐሺን ያዘ። ሆኖም በሳርጎን ልጅ በሪሙሽ ላይ የማርሐሺ ገዢ አባልጋማሽና ሻለቃው ሲድጋው ከአዋን ገዥ ኤማህሲኒ ጋር እንደገና በአመጽ ተነሥተው ተሸነፉ። የሪሙሽም ተከታይ ናራም-ሲን ደግሞ ማርሐሲን ድል አደረገ።

ከዚህም በኋላ በኡር መንግሥት ዘመን የኡር ንጉሥ ሹልጊ በ18ኛው ዓመት ሴት ልጁን ኒያሊሚዳሹን ለማርሐሺ ንጉሥ ሊባኑክሻባሽ በጋብቻ ስምምነት ሰጣት። ይሁንና ይህ ሰላም አጭር ነበር፤ የሹልጊ ተከታይ አማር-ሲን በማርሐሺ አዲስ ንጉሥ በአርዊሉክፒ ላይ እንደ ዘመተ ይመዝገባልና።

ባቢሎን ንጉሥ ሐሙራቢ ፴ኛው የዓመት ስም ሐሙራቢ የኤላምን ሠራዊት እንዲሁም ከማርሐሺ፣ ሱባርቱ፣ ጉቲዩም፣ ቱፕሊያሽ (ኤሽኑና) እና ከማጊዩም ጠረፎች የተሰበሰበውን ብዛት በዘመቻ ያሸነፈበት ዓመት ይባል ነበር።