ከ«ኢየሱስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
r2.7.2) (Robot: Modifying pa:ਇਸਾ ਮਸੀਹ to pa:ਈਸਾ ਮਸੀਹ
r2.7.2) (ሎሌ መጨመር: pfl:Jesus von Nazaret
መስመር፡ 223፦ መስመር፡ 223፦
[[pap:Hesus]]
[[pap:Hesus]]
[[pdc:Yeesus Grischdus]]
[[pdc:Yeesus Grischdus]]
[[pfl:Jesus von Nazaret]]
[[pih:Jesus]]
[[pih:Jesus]]
[[pl:Jezus Chrystus]]
[[pl:Jezus Chrystus]]

እትም በ18:26, 12 ዲሴምበር 2012

በ14ኛው ከፍለ ዘመን መሰራቱ የሚታመን የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተክርቲያን ተከታዮች እምነት ይህ ምስል የእየሱስና የማሪያም ምስል ነው ብለው ያምናሉ

ኢየሱስ (ዕብራይስጥ: ישוע ፣ የሹዓ) የክርስትና ሃይማኖት መሰረት ነው። ክርስቶስ ማለት በግሪክ ቋንቋ Χριστός ነው፤ ይህም መሢሕ (ከዕብራይስጥ ማሺያሕ ወይም 'የተቀባ') ማለት ነው። እየሱሰ በብዙ አብያተ ክርስትያናት፤ አምላክ እና ፈጣሪ ነው ተብሎ ይታመናል። እንዲሁም አንዳንድ ሃይማኖቶች የእግዚአብሔር መልዕክተኛ ነው ሲሉ አንዳንዶቹ ደግሞ ነቢይ ነው ብለው ያምናሉ።

የኢየሱስ ጥቅሶችና ትምህርቶች

አብያተ ክርስቲያን ቅዱስ ብለው የሚቆጠሩት 4 መጻሕፍት ወንጌሎች የኢየሱስን ሕይወት ታሪክ ይገልጻሉ።

በነዚህ ወንጌሎች መሠረት ኢየሱስ ሲያስተምር ብዙ ጥቅሶች ይገኛሉ። ለምሳሌ፦

«የአሕዛብ አለቆች እንዲገዙአቸው ታላላቆቹም በላያቸው እንዲሠለጥኑ ታውቃላችሁ። በእናንተስ እንዲህ አይደለም...» (ማቴ 20፡25)

በዚሁ ጥቅስ ኢየሱስ ዓለሙን እንደ ገለበጠ ተብሏል። በዚያን ግዜ ይሁዳ በባዕድ አረመኔ ሕዝብ ከባድ ገዥነት ሥር ነበረችና፣ የአይሁዶች ሊቃውንት ከትንቢት የተነሣ ከሮሜ ዕጅ የሚያድናቸውን መሢሕ ይጠብቁ ነበር። ይህ አይነት ትንቢት ቢገኝም ኢየሱስ ያንግዜ በጦርነት ስላላነሣ የአይሁድ መሪዎች ሊቀበሉት ፈቃደኛ አልነበሩም።

ደግሞ «እግዚአብሔር ምኑን ይፈልጋል?» ለሚለው ለዘመናት ፍልስፍና ጥያቄ በመመልስ ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን ትንቢተ ኢሳይያስ ውስጥ ይህን መልስ አገኝቶ ብዙ ግዜ ያጠቁመው ነበር፦

«ምሕረት እፈልጋለሁ እንጂ መሥዋዕት አይደለም።»

ለሚሰሙት ተከታዮቹ ግን አዲስ ጥያቄ ጠየቃቸው፣ እንዲህ ሲል፦

«ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?» (ማርቆስ 8:36)

በወንጌላት በኩል እጅግ በርካታ ተመሳሳይ ትምህርቶች በቀላሉ ሊነቡ ይቻላል።

ኢየሱስ ማን ነው?

ተዋሕዶ አብያተ ክርስትያናት እምነት ትምህርት፣ የኢየሱስ ሰብአዊና መለኰታዊ ባሕርይ አንድ (ተዋሕዶ) ነው። ከካልኬዶን ጉባኤ ጀምሮ ግን በሮማ ቤተክርስትያን ትምህርት ዘንድ በሁለት ልዩ ልዩ ሰብአዊና መለኰታዊ ባሕርዮች ተለይቷል። ኢየሱስ ወልድ ሆኖ ከሥላሴ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ) አንዱ ክፍል በመሆኑ አምላክ ነው በማለት ይስማማሉ። «ቃሉ ሥጋ ሆነ» ሲባል፣ ፈጣሪው ወደ ፍጥረቱ በሙሉ በመግባት ዓለሙን ለማዳን ኃይልና ፈቃድ እንዳለው ገለጸ ለማለት ነው።

ከዚህ በላይ ስለ ኢየሱስ ማንነት ብዙዎች አብያተ ክርስትያናት ከአዲስ ኪዳን ጠቅሰው እንደሚያስተምሩ፦

1. ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ከሁለት ሺህ ዓመት በፊት በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ አንድ እንግዳ ሰው ብቅ አለ፡፡ ይህ ሰው በአለም ውስጥ የተወለደ ቢሆንም፣ ልክ እንደማንኛውም ሰው ሰብአዊ ማንነት ቢኖረውም ተራ ሰው አልነበረም። ከድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ተፀንሶ ወደ ምድር የመጣው፣ በሰው አምሳል የተገለጠው ራሱ እግዚአብሔር ነበር፡፡ ይህ ሰው (የእግዚአብሔር ልጅ) ነበር (ሉቃስ 1፡26-35)፣ (ዮሐንስ 1፡1 እና ዮሐንስ 1፡14)።

2. ኢየሱስ ወደ ምድር የመጣው ለተለየ ተልእኮ ነበር።

  • የሰው ልጅ ከጠፋበት መንገድ ሊመልስ (ሉቃስ 19፡10)።
  • ከጨለማ ስልጣን ሊያድነን (ቆላሲያስ 1፡13)፡፡
  • ነፍሱን ለእኛ ቤዛ አድርጎ ሊሰጥ፤ ደሙን ከፍሎ ሊገዛን (ማቴ 20፡28)፡፡
  • በሕይወታችን ያለውን የሰይጣንን ሥራ ሊያፈርስ (1ዮሐ 3፡8)፡፡
  • የዘላለም ሕይወት ሊሰጠን (1ዮሐ 5፡11፣12)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 3፡16፣17 እና ዮሐንስ 10፡10 ይመልከቱ፡፡
  • አዲስ ልደት በመስጠት የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ሊያደርገን (ዮሐ 1፡12)፡፡ በተጨማሪ 1ዮሐ 3፡1.2 ይመልከቱ
  • ከአብ ጋር የነበረንን ሕብረት ለማደስ (1ዮሐ 1፡3)።

3. ኢየሱስ፣ እግዚአብሔር ምን እንደሚመስል ሊያሳየን መጣ (ዮሐ 14፡7-11)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 1፡18 ይመልከቱ።

  • የእግዚአብሔርን ፍቅር አሳየን (1ዮሐ 4፡9፣10)፡፡ በተጨማሪ ሮሜ 5፡8 ይመልከቱ።
  • የእግዚአብሔርን ኃይል አሳየን፣ የታመሙትን፣ ሽባዎችን እና አይነስውራንን ፈወሰ (ማቴ 4፡24)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 9፡1-7 ይመልከቱ።
  • ርኩሳን መናፍስትን አስወጣ (ማር 1፡34)፡፡ በተጨማሪ ማርቆስ 5፡1-17 ይመልከቱ።
  • ተአምራትን አደረገ (ማር 4፡37-41)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 6፡1-21 ይመልከቱ።
  • ሙታንን አስነሳ (ዮሐ 11፡43፣44)፡፡

4. ኢየሱስ መከራችንን ተቀበለ ኢየሱስ በምድር ሕይወቱ እኛ የምንቀበለውን የሕይወት ችግሮች በሞላ አይቷል፤ ስለዚህም ሊራራልን ይችላል። (ዕብ 4፡15)፡፡ በተጨማሪ ማቴዎስ 8፡17 ይመልከቱ።

5. ኢየሱስ ስለእኛ በመስቀል ላይ ሞተ ኃጢአተኛ ሰዎች፣ ኢየሱስን እንደ ወንጀለኛ ከእንጨት በተሰራ መስቀል ላይ ቸነከሩት፡፡ ራሱን ከዚህ ማዳን ቢችልም፣ አላደረገውም፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር አለሙን የሚያድነው በእርሱ የመስቀል ላይ ሞት ነበርና፡፡ ስዚህ ኢየሱስ ስለ እኛ ሞተ! (ማር 15፡16-39 ያንብቡ) (1ጴጥ 2፡24)፡፡ በተጨማሪ ኢሳያስ 53፡5፣6 ያንብቡ፡፡

6. ኢየሱስ ስለእኛ ከሙታን መካከል ተነሳ ከሦስት ቀን የመቃብር ቆይታ በኃላ እግዚአብሔር ልጁን ከሙታን መካከል አስነሳው! (ማቴዎስ 28 ያንብቡ)፡፡ ትንሳኤውም ጭምር ለእኛ ሲል ነበር፡፡ (ኤፌ 2፡4-6)፡፡ በተጨማሪ ሮሜ 6፡4 ያንብቡ፡፡

7. ኢየሱስ ለእኛ የሰማይን ደጅ ከፈተልን በምድር ላይ የነበረውን ሥራ በፈፀመ ጊዜ ኢየሱስ ወደአባቱ ዘንድ ወደሰማይ አረገ፡፡ ይህም ጭምር ለእኛ ነበር፡፡ ምክንያቱም አሁንና ለዘላለሙ ከእርሱ ጋር አብረን ለመኖር ወደ እግዚአብሔር መገኛ የምንሄድበት መንገድ ከፍቶልናል፡፡ (ዕብ 10፡19-22)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 14፡1-3 ይመልከቱ። ለተጨማሪ መረጃ የሚከተለውን አድራሻ ይጎብኙ፡ http://bible-question-and-answer.blogspot.com/2012/02/blog-post.html

ተጨማሪ ማጣቀሻዎች:-

መለጠፊያ:Link FA መለጠፊያ:Link FA መለጠፊያ:Link FA መለጠፊያ:Link FA መለጠፊያ:Link FA መለጠፊያ:Link FA መለጠፊያ:Link FA መለጠፊያ:Link FA