ከ«አብርሀም ሊንከን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
r2.7.3) (Robot: Modifying it:Abramo Lincoln to it:Abraham Lincoln
r2.7.2) (ሎሌ መጨመር: pag:Abraham Lincoln
መስመር፡ 106፦ መስመር፡ 106፦
[[oc:Abraham Lincoln]]
[[oc:Abraham Lincoln]]
[[os:Линкольн, Авраам]]
[[os:Линкольн, Авраам]]
[[pag:Abraham Lincoln]]
[[pam:Abraham Lincoln]]
[[pam:Abraham Lincoln]]
[[pap:Abraham Lincoln]]
[[pap:Abraham Lincoln]]

እትም በ16:11, 20 ፌብሩዌሪ 2013

አብርሀም ሊንከን

አብርሀም ሊንከን (እንግሊዝኛAbraham Lincolnየካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ የኖሩ) ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ።

የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዚ ብዛት ግን ለመደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ።

፲፰፻፴፰ ዓ.ም. የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጄምስ ፖልክሜክሲኮ ላይ ጦርነት ባደረገ ጊዜ አብርሀም ሊንከን የዚህን ጦርነት ተቃዋሚ ነበሩ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና አጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ።

ይህም የሆነ የሕዝቡ ብዛት በአገሩ ስሜን እየኖረ የሬፑብሊካን ደጋፊዎች ነበሩ። በስሜኑ ክፍላገሮች ደግሞ፣ ባርነት ከዚህ በፊት ተክለክሎ ነበር። በአሜሪካ ደቡብ በተገኙ ክፍላገሮች ግን ባርነት ገና የተለመደ ከመሆኑ በላይ በጥጥ የተመሠረተው የምጣኔ ሀብታቸው አስፈላጊነት መሰላቸው። ስለዚህ የባርነት ተቃዋሚ ሊንከን ፕሬዚዳንት መሆኑ በደቡብ ያሉት ክፍላገሮች ከአሜሪካ መገንጠላቸው ማለት ነበር። እንዲሁም ከምርጫው ቶሎ ተቀጥሎ ማዕረጉንም እንኳን ገና ሳይይዙ፣ ሳውዝ ካሮላይናታኅሣሥ ፲፪ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. መገንጠሏን አወጀች። በጥቂት ግዜ ውስጥ ሌሎች የደቡብ ክፍላገሮች እንዲህ አዋጁና በጥር ፳፭ ቀን ቴክሳስ ፯ኛው ሆነ። ከዚያ ቀጥሎ እነዚህ ፯ ክፍላገሮች በሞንትጎመሪ፣ አላባማ ተባብረው አዲሱ መንግሥት የአሜሪካ ኮንፌዴራት ክፍላገሮች (CSA) ተባሉ። በየካቲት ፳፮ ቀን ሊንከን የፕሬዚዳንትነቱን ማዕረግ በተቀበሉበት ቀን አገሩ በተግባር በሁለት ተከፋፍሎ ነበር። የደቡብ ፕሬዚዳንት ጄፈርሰን ዴቪስ ሆኑ። የደቡብ ክፍላገሮች ለጦርነት ተዘጋጁና ምሽጎች ከUSA ሠራዊት ሊይዙ ጀመር። በሚያዝያ ፭ ቀን ፎርት ሰምተር ምሽግ በሳውስ ካሮላይና በግፍ ስለ ተያዘ ጦርነቱ ጀመረ። ስለዚህ ሊንከን ከስሜኑ ፸፭ ሺ ሰዎች ለዘመቻ ጠሩ። ከዚህ በኋላ ሌላ አራት ደቡብ ክፍላገሮች ተገንጥለው ለCSA ተጨመሩ። የደቡብ ዋና ከተማ ለዋሺንግተን ዲሲ ቅርብ ወደ ሆነው ወደ ሪችሞንድ፣ ቪርጂንያ ተዛወረ።

በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ግዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ።

መለጠፊያ:Link FA መለጠፊያ:Link FA መለጠፊያ:Link GA መለጠፊያ:Link GA መለጠፊያ:Link GA