ከ«ራስ መኮንን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
Bot: Migrating 7 interwiki links, now provided by Wikidata on d:q2564998 (translate me)
Robot: Replacing category የኢትዮጵያ ታሪክ with ኢትዮጵያ በ19ኛው ክፍለ ዘመን
መስመር፡ 14፦ መስመር፡ 14፦
* ''ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ'' - [[ቀ.ኃ.ሥ.]] 1929 ዓ.ም - ገጽ 1፣ 2፡ 9-10
* ''ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ'' - [[ቀ.ኃ.ሥ.]] 1929 ዓ.ም - ገጽ 1፣ 2፡ 9-10
* ''አጤ ምኒልክ'' - [[ጳውሎስ ኞኞ]] 1984 ዓ.ም ገጽ 143፤ 160
* ''አጤ ምኒልክ'' - [[ጳውሎስ ኞኞ]] 1984 ዓ.ም ገጽ 143፤ 160
{{Link FA|fr}}


[[መደብ:የኢትዮጵያ ሰዎች]]
[[መደብ:የኢትዮጵያ ሰዎች]]
[[መደብ:የኢትዮጵያ ታሪክ]]
[[መደብ:ኢትዮጵያ በ19ኛው ክፍለ ዘመን]]

{{Link FA|fr}}

እትም በ19:25, 8 ፌብሩዌሪ 2014

ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል

ልዑል ራስ መኮንንሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት 1 ቀን 1844 ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ 14 ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተመንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ።
፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ።

ልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ "...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል..." እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል።

፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። ከአልቃሾቹም አንዱ ደግነታቸውን ለማስታወስ እንዲህ ብሎ አሟሸ፤-

«ስልከኛው ሲያረዳ ነገር ተሳሳተው፤ መኮንን አይደለም ድኃ ነው የሞተው»

ዋቢ መጻሕፍት

  • ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ - ቀ.ኃ.ሥ. 1929 ዓ.ም - ገጽ 1፣ 2፡ 9-10
  • አጤ ምኒልክ - ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም ገጽ 143፤ 160

መለጠፊያ:Link FA