ከ«የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ድምፅ መልዕክት ወደ ንግሥት ቪክቶሪያ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
Robot-assisted disambiguation: እንግሊዝ - Changed link(s) to ዩናይትድ ኪንግደም
No edit summary
መስመር፡ 1፦ መስመር፡ 1፦
[[File:የዳግማዊ ዓፄ ምንሊክ ድምጽ መልዕክት ወደ ቪክቶሪያ.ogg|right|thumb|የዓፄ ምኒልክ የድምጽ መልዕክት]]
[[File:የዳግማዊ ዓፄ ምንሊክ ድምጽ መልዕክት ወደ ቪክቶሪያ.ogg|right|thumb|የዓፄ ምኒልክ የድምጽ መልዕክት]]
'''የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ድምፅ መልዕክት ወደ ንግሥት ቪክቶሪያ''' በ[[1891|፲፰፻፺፩]] ዓ.ም. [[ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ]] ለእንግሊዟ [[ንግሥት ቪክቶሪያ]] በ[[ፎኖግራፍ]] ድምፅ መቅርጫ አድርገው የላኩት የድምፅ ደብዳቤ ነበር<ref>http://paperspast.natlib.govt.nz/cgi-bin/paperspast?a=d&d=HBH18990331.2.38</ref>። ደብዳቤው በሰላምታና በመልካም ምኞት ላይ ሲያተኩር፣ እንዲሁም በቅርቡ የተካሄደውን የ[[ዩናይትድ ኪንግደም|እንግሊዝ]]ን በ[[ሱዳን]] ላይ ድል በማስመልከት የ[[መተማ]] ከተማ የኢትዮጵያ እንደሆነ ንግሥቲቱ እንዲወስኑ ያሳውቃል። ከጎን ፋይሉ ቀርቧል። ከዚህ በታች ደግሞ መልዕክቱ ቃል በቃል ምን እንደሚል በጽሑፍ ቀርቧል።
'''የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ድምፅ መልዕክት ወደ ንግሥት ቪክቶሪያ''' በ[[1891|፲፰፻፺፩]] ዓ.ም. [[ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ]] ለእንግሊዟ [[ንግሥት ቪክቶሪያ]] በ[[ፎኖግራፍ]] ድምፅ መቅርጫ አድርገው የላኩት የድምፅ ደብዳቤ ነበር<ref>http://paperspast.natlib.govt.nz/cgi-bin/paperspast?a=d&d=HBH18990331.2.38</ref>። ይህንን መልክት በ[[አዲስ አበባ]] የ[[ብሪታኒያ]]ው ዋና መላክተኛ ጆን ሌን ሃሪንግቶን [[ግንቦት ፳፯]] ቀን [[1891|፲፰፻፺፩]] ዓ/ም ለብሪታኒያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በላከው ደብዳቤ መረከቡን ሲገልጽ በቅጅው ላይ የ[[እቴጌ ጣይቱ]]ም ድምጽ አብሮ መቀረጹን ይገልጻል።
የጃንሆይ ምኒልክ ደብዳቤ በሰላምታና በመልካም ምኞት ላይ ሲያተኩር፣ እንዲሁም በቅርቡ የተካሄደውን የ[[ዩናይትድ ኪንግደም|እንግሊዝ]]ን በ[[ሱዳን]] ላይ ድል በማስመልከት የ[[መተማ]] ከተማ የኢትዮጵያ እንደሆነ ንግሥቲቱ እንዲወስኑ ያሳውቃል። ከጎን ፋይሉ ቀርቧል። ከዚህ በታች ደግሞ መልዕክቱ ቃል በቃል ምን እንደሚል በጽሑፍ ቀርቧል።


<blockquote>«እኔ ዳግማዊ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ እጅግ ለከበሩ ወዳጃችን ቪክቶሪያ የታላቅ የእንግሊዝ ሕዝብ የሕዝብ ነገሥታት መድኃኔ ዓለም ጤና ይስጥልኝ እላለሁ።<br/><br/>
<blockquote>«እኔ ዳግማዊ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ እጅግ ለከበሩ ወዳጃችን ቪክቶሪያ የታላቅ የእንግሊዝ ሕዝብ የሕዝብ ነገሥታት መድኃኔ ዓለም ጤና ይስጥልኝ እላለሁ።<br/><br/>

እትም በ17:43, 17 ማርች 2014

የዓፄ ምኒልክ የድምጽ መልዕክት

የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ድምፅ መልዕክት ወደ ንግሥት ቪክቶሪያ፲፰፻፺፩ ዓ.ም. ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ለእንግሊዟ ንግሥት ቪክቶሪያፎኖግራፍ ድምፅ መቅርጫ አድርገው የላኩት የድምፅ ደብዳቤ ነበር[1]። ይህንን መልክት በአዲስ አበባብሪታኒያው ዋና መላክተኛ ጆን ሌን ሃሪንግቶን ግንቦት ፳፯ ቀን ፲፰፻፺፩ ዓ/ም ለብሪታኒያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በላከው ደብዳቤ መረከቡን ሲገልጽ በቅጅው ላይ የእቴጌ ጣይቱም ድምጽ አብሮ መቀረጹን ይገልጻል።

የጃንሆይ ምኒልክ ደብዳቤ በሰላምታና በመልካም ምኞት ላይ ሲያተኩር፣ እንዲሁም በቅርቡ የተካሄደውን የእንግሊዝን በሱዳን ላይ ድል በማስመልከት የመተማ ከተማ የኢትዮጵያ እንደሆነ ንግሥቲቱ እንዲወስኑ ያሳውቃል። ከጎን ፋይሉ ቀርቧል። ከዚህ በታች ደግሞ መልዕክቱ ቃል በቃል ምን እንደሚል በጽሑፍ ቀርቧል።

«እኔ ዳግማዊ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ እጅግ ለከበሩ ወዳጃችን ቪክቶሪያ የታላቅ የእንግሊዝ ሕዝብ የሕዝብ ነገሥታት መድኃኔ ዓለም ጤና ይስጥልኝ እላለሁ።

በሙሴ ሃሪንግቶን እጅ እጅግ የተዋበ ያማረ የንግሥት ፎኖግራፍ ሲደርስልኝ የከበሩ ንግሥት ድምፅ አጠገቤ ሆነው ስሰማ በብዙ ደስታ አደመጥኩ።

ለኛና ለመንግሥቴ ስለ መልካም ምኞትዎ እግዚአብሔር ያመስግንዎ። ለርስዎ ዕድሜና ጤና ለሕዝብዎ ሰላምና ዕረፍት እግዚአብሔር ይስጥዎ። በሁለታችን ሕዝብ መካከል ያለውን ጉዳይ ሁሉ ከሙሴ ሃሪንግቶን ጋር ተነጋገርኩ። እርሱም አሁን ወደ እንግሊዝ አገር እመለሳለሁ ቢለኝ ጉዳያችንን ሁሉ አቃንተህ ብትመለስ ደስ ይለኛል ብዬ ነገርኩት። አሁን ደግሞ ንግሥት በደህና እንዲቀበሉት።

ደግሞ የመተማ ነገር የእኛ ታላቁ ንጉሣችንና ብዙ የአገራችን ሰዎች ስለኃይማኖታቸው እልህ ብለው የሞቱበትን ለሙሴ ሃሪንግቶን ነግረነዋልና ይህንን ከተማ የእንግሊዝ መንግሥት እንዲያውቅልን እርስዎ ይረዱናል ብዬ ተስፋ አለኝ።

ኢትዮጵያ እና የእንግሊዝ አገር በሰላምና በፍቅር እንዲኖሩ እግዚአብሔር ይርዳን ብዬ ለታላቅ ሕዝብዎ የክብር ሰላምታዬን አቀርባለሁ።»

ማጣቀሻ

  1. ^ http://paperspast.natlib.govt.nz/cgi-bin/paperspast?a=d&d=HBH18990331.2.38