ከ«ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 15፦ መስመር፡ 15፦
ከምዕራፍ ፳፱ «[[ሕገ መንግሥት]] ስለ ማቆማችን» ያለው ፍሬ ነገር፦
ከምዕራፍ ፳፱ «[[ሕገ መንግሥት]] ስለ ማቆማችን» ያለው ፍሬ ነገር፦


:«[[ሕግ]] ለሰው ሁሉ የበለጠ የሚጠቅም መሆኑን ማንም አይስተውም። መከበርም መጠቀምም የሚገኙት ከሕግ መተካከል የተነሣ ነው። መዋረድም መጐዳትም የሚመጡት ከሕግ መጓደል የተነሣ ነው። ግፍና በደልም የሚበዙት ሕግ ባለመቅፕሙ ነው።
:«[[ሕግ]] ለሰው ሁሉ የበለጠ የሚጠቅም መሆኑን ማንም አይስተውም። መከበርም መጠቀምም የሚገኙት ከሕግ መተካከል የተነሣ ነው። መዋረድም መጐዳትም የሚመጡት ከሕግ መጓደል የተነሣ ነው። ግፍና በደልም የሚበዙት ሕግ ባለመቀሙ ነው።
:[[እግዚአብሔር]] ከፍጥረት ሁሉ በላይ ሆኖ፤ በቃሉ ብቻ ማዘዝ የማይቸግረው ሲሆን ፡ ሕግን መሥራቱ ሕግ ለዓለም ሁሉ የበላይ ገዥ እንዲሆን ስለ ዐወቀ ነው።
:[[እግዚአብሔር]] ከፍጥረት ሁሉ በላይ ሆኖ፤ በቃሉ ብቻ ማዘዝ የማይቸግረው ሲሆን ፡ ሕግን መሥራቱ ሕግ ለዓለም ሁሉ የበላይ ገዥ እንዲሆን ስለ ዐወቀ ነው።
:ከሰውም ትክክለኛ ለመባል የሚገባው በማናቸውም ረገድ ቢሆን፤ ዋናውን አሳብ አዝልቆ ሲሆን ሰውን ሁሉ በሙሉ፤ ሳይሆንም የሚበዛውን ለመጥቀም በተሰጠው [[ዕውቀት]] የሚጣጣርና የሚችል ሲሆን ነው።»
:ከሰውም ትክክለኛ ለመባል የሚገባው በማናቸውም ረገድ ቢሆን፤ ዋናውን አሳብ አዝልቆ ሲሆን ሰውን ሁሉ በሙሉ፤ ሳይሆንም የሚበዛውን ለመጥቀም በተሰጠው [[ዕውቀት]] የሚጣጣርና የሚችል ሲሆን ነው።»

እትም በ13:59, 22 ኤፕሪል 2018

ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ አፄ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የጻፉት የሕይወታቸው ታሪክ ነው። በሁለት መጻሕፍት ታትሟል።

መጀመርያው መጽሐፍ ስለ ሕይወታቸው ከልደታቸው ከ1885 ዓም ጀምሮ እስከ 1929 ዓም እስከ ፋሺስት ወረራ ድረስ ይተርካል። በባስ፣ እንግላንድ በስደት ሳሉ ጽፈውት ከዚያው በፊት ስለ ነበረው የኢትዮጵያ አስተዳደርና ሥልጣኔ ደረጃ ከፍ ማለቱን ገልጸዋል።

በአንዱ ወሳኝ ምዕራፍ ፴ «የሕገ መንግሥትን ትርጓሜ ስለ ማስረዳት።» የበጅሮንድ ተክለ ሐዋርያትን ቃላት በሙሉ ጠቀሱዋቸው።

ሁለተኛው መጽሐፍ ከ1929 እስከ 1934 ዓም ያለውን ወቅት ይዘርዝራል፤ ይህም ኢትዮጵያ ከጣልያን ነጻ ሆና ወደ ዙፋናቸው የተመለሱበት ዘመን ነው።

የታተመው በ1965 ዓም ነበር።

ከመቅደም፦

«የእኔንም የሕይወት ታሪክ አንዳንድ ሰዎች ባለማወቅና በመሳሳት ፡ ወይም በምቀኝነት ፡ እውነት አስመስለው ጽፈው ፤ ሌሎችን እንዲመስላቸው ለማድረግ በፈትኑ ፤ የውነተኛውን ነገር ከስፍራው ሊያናውጹት አይችሉም። »

ከምዕራፍ ፳፱ «ሕገ መንግሥት ስለ ማቆማችን» ያለው ፍሬ ነገር፦

«ሕግ ለሰው ሁሉ የበለጠ የሚጠቅም መሆኑን ማንም አይስተውም። መከበርም መጠቀምም የሚገኙት ከሕግ መተካከል የተነሣ ነው። መዋረድም መጐዳትም የሚመጡት ከሕግ መጓደል የተነሣ ነው። ግፍና በደልም የሚበዙት ሕግ ባለመቀሙ ነው።
እግዚአብሔር ከፍጥረት ሁሉ በላይ ሆኖ፤ በቃሉ ብቻ ማዘዝ የማይቸግረው ሲሆን ፡ ሕግን መሥራቱ ሕግ ለዓለም ሁሉ የበላይ ገዥ እንዲሆን ስለ ዐወቀ ነው።
ከሰውም ትክክለኛ ለመባል የሚገባው በማናቸውም ረገድ ቢሆን፤ ዋናውን አሳብ አዝልቆ ሲሆን ሰውን ሁሉ በሙሉ፤ ሳይሆንም የሚበዛውን ለመጥቀም በተሰጠው ዕውቀት የሚጣጣርና የሚችል ሲሆን ነው።»