ከ«ክርስትና» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 26፦ መስመር፡ 26፦


==ቋንቋዎች==
==ቋንቋዎች==
ኢየሱስ የሰበከው በተለይ በ[[አረማይስጥ]]ና በ[[ዕብራይስጥ]] እንደ ነበር ይታመናል። [[ግሪክኛ]] ደግሞ በዙሪያው በሰፊ ይነገር ነበርና የአዲስ ኪዳን መጀመርያ የምናውቀው ቅጂ ግሪክኛ ነው። በሉቃስና ዮሐንስ ወንጌላት ዘንድ በመስቀል የተጻፉት ልሳናት ዕብራይስጥ፣ ግሪክኛና [[ሮማይስጥ]] ስለ ሆኑ እነዚህም ለዚያው ይከበራሉ። አዲስ ኪዳን በኋላ የተተረጎመባቸው ሌሎች ልሳናት ደግሞ እንደ ክቡራን ቋንቋዎች ተቆጠሩ፤ [[ግዕዝ]]፣ [[ቅብጥኛ]]፣ [[አርሜንኛ]]፣ [[ጥንታዊ ስላቭኛ]] እና ሌሎች በአብያተ ክርስትያናት መደበኛ ሆኑ። በአሁኑ ጊዜ አዲስ ኪዳን ወይም ቢያንስ ወንጌል በብዙ ሺህ የሰው ልጅ ቋንቋዎች ተተርጎመዋል።
ኢየሱስ የሰበከው ወንጌል በተለይ በ[[አረማይስጥ እንደ ነበር ይታመናል። [[ግሪክኛ]] ደግሞ በዙሪያው በሰፊ ይነገር ነበርና የአዲስ ኪዳን መጀመርያ የምናውቀው ቅጂ ግሪክኛ ነው። በሉቃስና ዮሐንስ ወንጌላት ዘንድ በመስቀል የተጻፉት ልሳናት ዕብራይስጥ፣ ግሪክኛና [[ሮማይስጥ]] ስለ ሆኑ እነዚህም ለዚያው ይከበራሉ። አዲስ ኪዳን በኋላ የተተረጎመባቸው ሌሎች ልሳናት ደግሞ እንደ ክቡራን ቋንቋዎች ተቆጠሩ፤ [[ግዕዝ]]፣ [[ቅብጥኛ]]፣ [[አርሜንኛ]]፣ [[ጥንታዊ ስላቭኛ]] እና ሌሎች በአብያተ ክርስትያናት መደበኛ ሆኑ። በአሁኑ ጊዜ አዲስ ኪዳን ወይም ቢያንስ ወንጌል በብዙ ሺህ የሰው ልጅ ቋንቋዎች ተተርጎመዋል።


{{መዋቅር-ሃይማኖት}}
{{መዋቅር-ሃይማኖት}}

እትም በ06:49, 20 ጁን 2018

ክርስትና'የሚለው ቃል መጽሐፍ ቅዱስ ላይ በቀጥታ የሌለ እና ከሦስተኛው ክፍለ ዘመን በኃላ ቃሉ አገልግሎት ላይ የዋለ ሲሆን በክርስቲያኖች ትምህርት የተመሠረተ እምነት ነው።

ክርስቲያን የሚለው ቃል ግን መጀመርያ የሚተረክበት አዲስ ኪዳን በተለይም ወንጌልየሐዋርያት ሥራ 11፥26 ነው። ስሙንም ያወጡት ጠላቶች ናቸው። "ክርስቲያን" ማለት ቅቡዓን፣ መሲሐውያን፣ ክርስቶሳውያን ማለት ነው።

በ41 ዓም የሮሜ ቄሣር ክላውዴዎስ «አይሁዶችን» ከሮሜ ከተማ ባሳደዳቸው ዘመን፣ ብዙዎቹ ክርስቲያኖች እንደ ነበሩ ይመስላል። ክርስቲያኖች በሮሜ መንግሥት ብዙ ጊዜ እስከ 303 አም ድረስ ከቄሣሮቹ መከራዎች ቢያገኙም፣ ሃይማኖቱ ግን ምንጊዜም እየተበዛ ነበር።

የአይሁዶች ትምህርት ግን በረቢ አኪቫ በን ዮሴፍ መሪነት በሌላ አቅጣቻ ሄዶ አዋልድ መጻሕፍት ከብሉይ ኪዳን አጠፉና ተልሙድ በተባለ ጽሑፍ አዳዲስ ትምህርቶችን ፈጠሩ። ስለዚህ የሮሜ ንጉሥ ቤስጳስያን የኢየሩሳሌምን ቤተ መቅደስ በ62 ዓም ካጠፋ በኋላ፣ አይሁድና እና ክርስትና እንደተለያዩ ሃይማኖቶች ተቆጥረዋል።

በ303 ዓም ክርስትና በሮሜ መንግሥት በጋሌሪዎስ ዘመን ሕጋዊ ሆነ። የሚቀጠለው ቄሳር ቆስጠንጢኖስ በመጋቢት 10 ቀን 313 ዓ.ም. በአዋጅ እሑድ ለሮማ ዜጎች ሁሉ ስለ ጣኦቱ አፖሎ የእረፍት ቀን እንዲሆንላቸው አዘዘ። በኋላ በ317 ዓም እርሱ የንቅያ ጉባኤ ጠራ፣ በዚህ ጉባኤ በዚያን ጊዜ በዕብራይስጥ የተገኙት ጸሐፍት ብቻ (አዋልድ መጻሕፍት ሳይሆኑ) በብሉይ ኪዳን እንዲቀበሉ ተስማሙ። ከጥቂት ዓመታት በኋላ ቆስጠንጢኖስ እራሱ ተጠመቀ። ከዚያስ የሮሜ ቤተ ክርስቲያን የአይሁዶችን «አጭር» ብሉይ ኪዳን የሚያጸድቀው ምንም ቢሆንም፣ እንደ አስርቱ ቃላት ሰንበት በቅዳሜ የከበሩት ሁሉ እንደ «አይሁዳውያን» ሀራ ጤቆች በአውሮጳ ይቆጠሩ ጀመር።

በዚህ ዘመን ያህል ብዙ ሌሎች ተወዳዳሪ ትምህርቶች በሮሜ መንግሥት ይሄዱ ነበር፣ በተለይም፦

አንድ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን (ካቴድራል) ውስጥ በውንቸስተር፣ እንግላንድ፣ ከፍተኛው መሠዊያ

ስለዚህ የንቅያ ጉባኤ የንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት ወሰነ። በዚህ ውስጥ ኢየሱስ ወልድ፣ ከአብ ጋራ አንድ ባሕርይ አለው ይላል። በ372 ዓም በተሰሎንቄ ዐዋጅ ቄሣሩ ጤዎዶስዮስ ይህን እምነት በሮሜ ግዛት ውስጥ የመንግሥት ሃይማኖት አደረገው፤ ብዙ የአረመኔ መቅደሶች ተፈረሱ። በሚከተለው ዓመት በ373 ዓም ፩ኛው የቁስጥንጥንያ ጉባኤ የጸሎተ ሃይማኖቱን ይፋዊ ቃላት ትንሽ ቀየሩ፤ በተለይም ስለ መንፈስ ቅዱስ ባሕርይና መለኰታዊነት በይበልጥ የሚገልጹ ቃላት ተጨመሩ።

ከዚያ የተነሣ ወደፊት ቄሣሮች በማንም ሰዓት ጉባኤ በመጥራት ይፋዊ የመንግሥት ሃይማኖት ቀይረው በፍጹም ሊያባልሹት ይቻላል የሚል ጭንቀት ነበር። በተለይ ኢየሱስ «ከአብ ጋር አንድ ባሕርይ አለው» ቢልም፣ ሆኖም ሁለት ልዩ ልዩ ጸባዮች አሉት የሚሉ አስተማሪዎች ሲቀርቡ፣ ይህ ኢየሱስ በሁለት ልዩ ልዩ ጸባዮች ተለይቷል ማለታቸው ወደፊት ቄሣሮቹ በተንኮላቸው ብዛት የመለኮታዊነቱን ጸባይ በይፋ አስለይተው ወደፊትም አንዱን ጸባይ መካድ ይችላሉና የሃይማኖት ጽሑፉን እንደገና ቀይረው 'ተራ ሰው ብቻ መሆኑ የሮሜ ይፋዊ እምነት ነው' ማለት ይችላሉ የሚል ጭንቀት ተነሣ። የንቅያ (ቁስጥንጥንያ የ373 ዓም) ጸሎተ ሃይማኖት ግን እስካሁን ድረስ ምንም ቃል ሳይቀየር በአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ (ካቶሊክተዋሕዶኦርቶዶክስ እና ፕሮቴስታንት) ይደገፋል።

ኢየሱስ አንድ «ተዋሕዶ» ጸባይ (ሰውና አምላክ) ያመነበት ወገን እንዲህ ካልሆነ ፈጣሪ ወደ ፍጥረቱ በፍጹምነት ተዋሕዶ ካልገባ በቀር የሰውን ልጅ አያድንም ነበር ባዮች ነበሩ። ነገር ግን የኢየሱስ «ሁለት ጸባዮች» ትምህርት ወዳጅ ወገን በመጨረሻ በፓፓ ኬልቄዶን ጉባኤ (443 አም) ስለ ተቀበለ፣ የሮሜ ፓፓ ከሌሎቹ ጳጳሳት (የእስክንድርያ፣ የአንጾኪያ ጳጳሳት) ተለያየ። እስካሁንም ድረስ ተዋሕዶ የተባሉት አብያተ ክርስቲያናት መጀመርያ ፫ቱ ጉባኤዎች (ንቅያ፣ ቁስጥንጥንያ፣ ኤፌሶን) ብቻ የሚቀበሉ ናቸው እንጂ የኬልቄዶን ጉባኤ አይቀበሉም።

እስከ 777 ዓም ድረስ በጥምቀት ሥርዓት ወደ ክርስትና የገቡት በጠቅላላ በፈቃደኝነትና በሰላም ነበር። ከነዚህ መካከል ብዙ ሕዝቦች ክርስትናን ተቀበሉ (የክርስትና መስፋፋት ይዩ።) በ777 ዓም ግን የፍራንኮች ንጉሥ ካሮሉስ ማግኑስሳክሶኖች ብሔር (በጀርመን የቀሩትን ሕዝብ) በግድና በዛቻ አስጠመቁዋቸው። ጀርመኖች ደግሞ በበኩላቸው ዞረው የባልቲክ ቋንቋ ተናጋሪ ነገዶችን (በተለይ ላትቪያሊትዌኒያ እና የቀድሞው ፕሩሳውያን) በጨካኝ ጦሮች አስጠመቁዋቸውና እንደ ባርዮች ያህል አደረጉዋቸው። ከነዚዎች ጉዳዮች በስተቀር ግን በክርስትና ታሪክ በአጠቃላይ አብዛኞቹ ብሔሮች የገቡት በሰላምና በፈቃደኝነት ሆኖዋል።

ቋንቋዎች

ኢየሱስ የሰበከው ወንጌል በተለይ በ[[አረማይስጥ እንደ ነበር ይታመናል። ግሪክኛ ደግሞ በዙሪያው በሰፊ ይነገር ነበርና የአዲስ ኪዳን መጀመርያ የምናውቀው ቅጂ ግሪክኛ ነው። በሉቃስና ዮሐንስ ወንጌላት ዘንድ በመስቀል የተጻፉት ልሳናት ዕብራይስጥ፣ ግሪክኛና ሮማይስጥ ስለ ሆኑ እነዚህም ለዚያው ይከበራሉ። አዲስ ኪዳን በኋላ የተተረጎመባቸው ሌሎች ልሳናት ደግሞ እንደ ክቡራን ቋንቋዎች ተቆጠሩ፤ ግዕዝቅብጥኛአርሜንኛጥንታዊ ስላቭኛ እና ሌሎች በአብያተ ክርስትያናት መደበኛ ሆኑ። በአሁኑ ጊዜ አዲስ ኪዳን ወይም ቢያንስ ወንጌል በብዙ ሺህ የሰው ልጅ ቋንቋዎች ተተርጎመዋል።

: