ከ«መጽሐፍ ቅዱስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 1፦ መስመር፡ 1፦
መጽሐፍ ቅዱስ ነብያት እና ታሪካውያን የጻፉት የክርስትና እና የአይሁዳውያን መጽሓፍ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በ[[ብሉይ ኪዳን]]ና በ[[አዲስ ኪዳን]] ተከፍሎ 81 መጻሕፍት ያሉት ሲሆን በአንዳንድ እምነቶች ደግሞ 66 ክፍል ብቻ ነው አሉት ብለው ያምናሉ። ከነ[[ዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት]]ም ጋራ የመጻሕፍት ቁጥር 81 ነው። ዝርዝሩን እንመጣበታለን። መጽሐፍ ቅዱስ ከመቶ 25% የአምላክ ንግግር፣ ከመቶ 25 % የነብያት ንግግር እና ከመቶ 50 % የታሪክ ጽሐፍያን ንግግር ይዟል።
መጽሐፍ ቅዱስ ነብያት እና ታሪካውያን የጻፉት የክርስትና እና የአይሁዳውያን መጽሓፍ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በ[[ብሉይ ኪዳን]]ና በ[[አዲስ ኪዳን]] ተከፍሎ 81 መጻሕፍት ያሉት ሲሆን በአንዳንድ እምነቶች ደግሞ 66 ክፍል ብቻ ነው አሉት ብለው ያምናሉ። ከነ[[ዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት]]ም ጋራ የመጻሕፍት ቁጥር 81 ነው። ዝርዝሩን እንመጣበታለን። መጽሐፍ ቅዱስ ከመቶ 25% የአምላክ ንግግር፣ ከመቶ 25 % የነብያት ንግግር እና ከመቶ 50 % የታሪክ ጽሐፍያን ንግግር ይዟል።


በዚህ ምህዋር እና ዐውድ ላይ “ቀኖና” ስንል የዶግማ ተቃራኒ የሆነውን የሚለወጠው ሕግ ወይም ሥርዓት ሳይሆን የቅዱሳን መጽሐፍትን “መለኪያ” ታሳቢና ዋቢ ያደረገ ነው። “ቀኖና” የሚለው ቃል የአማርኛችን ቃል “ካኑን” κανών ከሚል ግሪክ ቃል የተገኘ ነው፤ ይህም ቃል “ካና” κάννα ማለት “አሰመረ” “ለካ” ከሚል የኮይኔ ግሪክ ሥርወ-ቃል የተገኘ ሲሆን “ልኬት” ማለት ነው። አይሁዳውን በ 90 ድህረ-ልደት”AD” በጀሚኒያ ጉባኤ እንዲሁ ክርስቲያኖች በ 387 ድህረ-ልደት”AD” በካርቴጅ ጉባኤ በመጨመርና በመቀነስ ቀኖና እያሉ ሲያስወጡና ሲያስገቡ ነበር፤ በተለይ የካርቴጅ ጉባኤ መጽሐፍቶችን በሁለት ከፍለው ብሉይ እና አዲስ ብለው አስቀምጠውታል፤ እስቲ ይህንን ነጥብ በነጥብ እንመልከት፦
== የመጽሐፍ ቅዱስ ምንነት ==
በ[[እንግሊዝኛ]] ቋንቋ የተለመደው «ባይብል» የሚለው ቃል ከጥንቱ [[የኮይነ ግሪክኛ]] ቋንቋ የተወሰደ ሲሆን ቃሉ የተገኘበት τὰ βιβλία /ታ ቢብሊያ/ የሚለው ሀረግ «መጽሐፍቱ» ወይም «ትንንሽ መጽሐፍት» ተብሎ ሊተረጎም ይችላል። የዚሁም ቃል መነሻ ከግሪኩ ስም Βύβλος /ቢውብሎስ/ ([[ፓፒሩስ]] ወይም [[ቄጠማ]]፣ የ[[ወረቀት]] ተክል) ሲሆን ይሄ ቃል «ፓፒሩስ» ከተነገደበት ከተማ [[ጌባል]] / ቢውብሎስ ስም መጣ።


ነጥብ አንድ
መጽሐፍ ቅዱስ ለ[[አይሁድና]] [[ክርስትና]] እምነት የእምነት መሰረት የሆኑ ትናንሽ መጽሐፍትን የያዘ አንድ ጥራዝ ነው። በተለምዶ «ብሉይ ኪዳን» በመባል የሚጠራውና በአይሁዳውያን በ24 እና በክርስቲያኖች በ39 መጽሐፍት የሚከፈለው የመጽሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያ ክፍል በመጀመሪያ በአብዛኛው የተጻፈው በጥንታዊው የ[[ዕብራይስጥ]] ቋንቋ ሲሆን የተጻፉበት ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት የተወሰኑ መቶ አመታት ቀደም ብሎ እንደሆነ ይነገራል። እነዚህን መጽሐፍት የጻፉት በወቅቱ የነበሩ የታመኑ አይሁዳውያን ወይም [[እስራኤላውያን]] ናቸው። የመጨረሻዎቹን 27 መጻሕፍት በግሪክኛ የጻፏቸው ክርስቲያኖች ሲሆኑ «አዲስ ኪዳን» በመባል በሰፊው ይታወቃሉ። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኘው ማስረጃም ሆነ በጣም ጥንታዊ የሆኑት ወጎች እንደሚጠቁሙት እነዚህ 66 መጻህፍት የተጻፉት ግብጽ ኃያል ከነበረችበት ጊዜ አንስቶ [[ሮም]] የዓለም ኃያል መንግስት እስከ ነበረችበት ዘመን ባሉት 1600 ዓመታት ውስጥ ነው።
“ብሉይ ኪዳን”
ብሉይ ኪዳን ላይ ስላሉት መጽሐፍት የተለያዩ አንጃዎች አንድ አቋም የላቸውም፤ እነርሱን በተናጥን እስቲ እንይ፦


A. “የፕሮቴስታንት ቀኖና”
በ[[ካቶሊክ ቤተክርስቲያን]] እምነት መሰረት ከ66ቱ መጽሐፍት በተጨማሪ የተካተቱ የተወሰኑ መጽሐፍት ሲኖሩ፣ በ[[ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን]] እነዚህ ተጨማሪ መጻሕፍት (ዲዩቴሮካኖኒካል በመባልም ይታወቃሉ) በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተካተቱትን መጻሕፍት ቁጥር ወደ 81 ያደርሱታል።
ፕሮቴስታንት የሚቀበለው ሁሉም ጋር ተቀባይነት ያለው አቆጣጠር
የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት 39 ናቸው፤ እነርሱም፦
1. ኦሪት ዘፍጥረት
2. ኦሪት ዘጸአት
3 ኦሪት ዘኁልቁ
4. ኦሪት ዘሌዋውያን
5. ኦሪት ዘዳግም
6. መጽሐፈ ኢያሱ
7. መጽሐፈ መሳፍንት
8. መጽሐፈ ሩት
9. መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ
10. መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ
11. መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ
12. መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ
13. ዜና መዋዕል ቀዳማዊ
14. ዜና መዋዕል ካልዕ
15. መጽሐፈ ዕዝራ
16. መጽሐፈ ነህምያ
17. መጽሐፈ አስቴር
18. መጽሐፈ ኢዮብ
19. መዝሙረ ዳዊት
20. መጽሐፈ ምሳሌ
21. መጽሐፈ መክብብ
22. መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን
23. ትንቢተ ኢሳይያስ
24. ትንቢተ ኤርምያስ
25. ሰቆቃው ኤርምያስ
26. ትንቢተ ሕዝቅኤል
27. ትንቢተ ዳንኤል
28. ትንቢተ ሆሴዕ
29. ትንቢተ አሞጽ
30. ትንቢተ ሚክያስ
31. ትንቢተ ኢዮኤል
32. ትንቢተ አብድዩ
33. ትንቢተ ዮናስ
34. ትንቢተ ናሆም
35. ትንቢተ ዕንባቆም
36. ትንቢተ ሶፎንያስ
37. ትንቢተ ሐጌ
38. ትንቢተ ዘካርያስ
39. ትንቢተ ሚልክያስ ናቸው።


B. “የአይሁዳውያን ቀኖና”
ከክርስቶስ ስብከት ቀጥሎ ምዕመናን የሆኑት ለረጅም ዘመን ተጨማሪ መጻሕፍቱን ከነ[[መጽሐፈ ሄኖክ]]ና [[ኩፋሌ]] ያንብቡ ነበር። የ[[አይሁድ]] [[ሰንሄድሪን]] ረቢዎች በ100 ዓ.ም. አካባቢ በተለይም ረቢ [[አኪቫ በን ዮሴፍ]] እነዚህን ተጨማሪ መጻሕፍት ከዕብራይስጥ ቅጂ አጠፉ። እስካሁንም ድረስ በዕብራይስጥ ትርጉም አይታወቁም። አዲስ ኪዳን ከተጻፈ በኋላ፣ ብዙ አጠያያቂ ወንጌሎችና የሌሎች እምነቶች ጽሑፎች ደግሞ ሊሠራጩ ጀመር። [[ግኖስቲክ]] የተባለው እምነት ተከታዮች በተለይ ብዙ ሥነ ጽሑፍ ፈጠሩ፣ ይህ ግን ከኦርቶዶክስ ወንጌል የተዛቡ ትምህርቶች ነበር። በ170 ዓ.ም. በክርስትያኖች ዘንድ የቱ መጻሕፍት ትክክለኛ ቅዱሳን መጻሕፍት ናቸው? የሚል ጥያቄ ይነሣ ጀመር። [[መሊቶ ዘሳርዲስ]] የተባለ ጳጳስ በዚያን ጊዜ ወደ [[ኢየሩሳሌም]] መጻሕፍት ቤት ጉዞ አድርጎ የ ዕብራውያን መጻሕፍት ምን ምን እንደ ነበሩ ዘገበ። ተጨማሪ መጻሕፍቱ ከዚያ በፊት ስለ ጠፉ አልተዘገቡም። ስለዚህ ከዚህ በቀር ምንም ያልተዘረዘሩት ብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ትክክለኛ አይሆኑም የሚል ሀሣብ በ[[ሮሜ መንግሥት]] ክርስቲያኖች ተነሣ። ይህም የአይሁዶች [[ቀኖና]] በ[[ንቅያ ጉባኤ]] ([[317]] ዓ.ም.) በሮሜ መንግሥት ለክርስቲያኖች ጸና።
39 መጽሐፍት አይሁዳውያን እንደጎሮሳውያን አቆጣጠር በ 90 ድህረ-ልደት”AD” በጀሚኒያ 24 የቀኖና መጽሐፍት አርገዋቸዋል፤ አቆጣጠራቸው ግን ይለያል፦
1. መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ እና መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ አንድ መጽሐፍ ሻሙኤል ብለው፣
2. መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ እና መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ አንድ መጽሐፍ መላክሂም ብለው፣
3. ዜና መዋዕል ቀዳማዊ እና ዜና መዋዕል ካልዕ አንድ መጽሐፍ ሃያሚን ብለው፣
4. መጽሐፈ ዕዝራ እና መጽሐፈ ነህምያ አንድ መጽሐፍ አዝራ ብለው፣
5. ከሆሴዕ እስከ ሚልኪያስ ያሉት 12 መጽሐፍት አንድ መጽሐፍ ትሬአሳር ብለው ይቆጥሩታል።

ከሆሴዕ እስከ ሚልኪያስ ያሉት በአንድ የተጣፉትን 11 መጽሐፍት እና የተጣፉትን 4 መጽሐፍት ስንደምር 15 ይሆናል፤ 15+24= 39 መጽሐፍት ይሆናሉ። አይሁዳውያን መጽሐፍቶቻቸውን “ታንካህ” תַּנַ”ךְ, ሲሉት የሶስቱ መጽሐፍት መነሻ ላይ ያሉት ቃላት መሰረት አርገው ነው፤ እነዚህም “ታ” תַּ ቶራህ፣ “ና” נַ ነቢኢም፣ “ካ” ךְ ኬቱዊም ናቸው። “ቶራህ” תּוֹרָה ማለት “ኦሪት” “ሕግ” “መርሕ” ማለት ነው፣ ከዘፍጥረት እስከ ዘዳግም ያሉትን ለማመልከት ይጠቀሙብታል።
“ነቢኢም” נְבִיאִים ማለት “ነቢያት” ማለት ሲሆን የኢሳያስ ትንቢት፣ የኤርሚያስ ትንቢት፣ የህዝቅኤል ትንቢት ወዘተ ለማመልከት ይጠቀሙብታል።
“ኬቱዊም” כְּתוּבִים ማለት “መጻሕፍት” ማለት ሲሆን የኢዮብ መጽሐፍ፣ የመዝሙር መጽሐፍ፣ የምሳሌ መጽሐፍ፣ የመክብብ መጽሐፍ፣ የመኃልየ መኃልይ መጽሐፍ ወዘተ ለማመልከት ይጠቀሙብታል።

C. “የካቶሊክ ቀኖና”
የሮማ ካቶሊክ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 46 ናቸው፤ ካቶሊክ በ 39 ላይ እራሳቸውን የቻሉ 7 ጭማሬ መጽሐፍት ሲኖራቸው እነዚህ ጭማሬ፦
1. መጽሐፈ ጦቢት፣
2. መጽሐፈ ዮዲት፣
3. መጽሐፈ ጥበብ፣
4. መጽሐፈ ሲራክ፣
5. መጽሐፈ ባሮክ፣
6. መጽሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ
7. መጽሐፈ መቃብያን ካልዕ ናቸው።

D. “የኦርቶዶክስ ቀኖና”
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 46 ናቸው፤ የብሉይ ኪዳን መደበኛ የቀኖና መጽሐፍት 39 ሲሆኑ ተጨማሪ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 18 ናቸው፤ ነገር ግን አቆጣረራቸው ልክ እንደ አይሁድ ይለያል። እራሳቸውን የቻሉ 10 ጭማሬ መጽሐፍት ሲኖራቸው እነዚህ ጭማሬ አቆጣጠራቸው፦
1. መጽሐፈ ሄኖክ፣
2. መጽሐፈ ኩፋሌ(ጁብሊይ)፣
3. መጽሐፈ ጦቢት፣
4. መጽሐፈ ዮዲት፣
5. መጽሐፈ ተግሣጽ፣
6. መጽሐፈ ጥበብ፣
7. መጽሐፈ ሲራክ
8. መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ቀዳማይ እና መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ካልዕ፣
9. መጽሐፈ መቃብያን ቀዳማይ እና መጽሐፈ መቃብያን ካልዕ፣
10. መጽሐፈ መቃብያን ሣልስ ናቸው።

ነባር መጽሐፍት ላይ በመቀነስ ተጨፍልቀው የሚቆጠሩ 2 መጽሐፍት ናቸው፤ እነርሱም፦
11. መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማይ እና መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ ናቸው፣
12. መጽሐፈ ዕዝራ ቀዳማይ እና መጽሐፈ ዕዝራ ካልዕ(ነህምያ) ናቸው።

ከነባር መጽሐፍት ጋር ተደምረው የሚቆጠሩ ደግሞ 8 መጽሐፍት ናቸው፤ እነርሱም፦
13. ከትንቢተ ኢሳይያስ ጋር የሚቆጠረው ጸሎተ ምናሴ ነው።
14. ከትንቢተ ኤርምያስ ጋር የሚቆጠሩ፦ ሰቆቃወ ኤርምያስ፣ ተረፈ ኤርምያስ፣ መጽሐፈ ባሮክ፣ ተረፈ ባሮክ ናቸው።
15. ከትንቢተ ዳንኤል ጋር የሚቆጠሩ መጽሐፈ ሶስና፣ ጸሎተ ሠለስቱ ደቂቅ እና ተረፈ ዳንኤል ናቸው።

ከ 39 ላይ 8 መጽሐፍት፦ ሳሙኤል ቀዳማይ፣ ሳሙኤል ካልዕ፣ መጽሐፈ ዕዝራ፣ መጽሐፈ ነህምያ፣ ትንቢተ ኢሳይያስ፣ ትንቢተ ኤርሚያስ፣ ሰቆቃው ኤርሚያስ እና ትንቢተ ዳንኤል ሲቀነሱ 31 መጽሐፍት ይሆናሉ። 31+15= 46 ይሆናል።

F. “የሰፕቱአጀንት ቀኖና”
የሰፕቱአጀንት የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 56 ናቸው፤ የሰፕቱአጀንት”LXX” በ 39 ላይ እራሳቸውን የቻሉ 17 ጭማሬ መጽሐፍት ሲኖራቸው እነዚህ ጭማሬ፦
1. መጽሐፈ ጦቢት፣
2. መጽሐፈ ዮዲት፣
3. መጽሐፈ ጥበብ፣
4. መጽሐፈ ሲራክ፣
5. መጽሐፈ ባሮክ፣
6. ተረፈ ኤርምያስ፣
7. ጸሎተ ሠለስቱ ደቂቅ፣
8. መጽሐፈ ሶስና፣
9. ቤልና ድራጎን፣
10. ጸሎተ ምናሴ፣
11.1ኛ መቃብያን፣
12. 2ኛ መቃብያን፣
13. 3ኛ መቃብያን፣
14. 4ኛ. መቃብያን፣
15. ዕዝራ ሱቱኤል፣
16. የአዛርያ ጸሎት፣
17. መዝሙር 151 ናቸው።

G. “የቩልጌት ቀኖና”
ጄሮም በ 382 ድህረ-ልደት በላቲን ቩልጌት ባዘጋጀው ደግሞ የመጽሐፍት ቀኖና 45 ናቸው፤ የቩልጌት በ 39 ላይ እራሳቸውን የቻሉ 6 ጭማሬ መጽሐፍት ሲኖራቸው እነዚህ ጭማሬ፦
1. መጽሐፈ ጦቢት፣
2. መጽሐፈ ዮዲት፣
3.1ኛ መቃብያን፣
4. 2ኛ መቃብያን፣
5. መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ቀዳማይ፣
6. መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ካልዕ


== የመጽሐፍ ቅዱስ ልዩ ባህርያት ==
== የመጽሐፍ ቅዱስ ልዩ ባህርያት ==

እትም በ23:22, 15 ኦገስት 2018

መጽሐፍ ቅዱስ ነብያት እና ታሪካውያን የጻፉት የክርስትና እና የአይሁዳውያን መጽሓፍ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በብሉይ ኪዳንና በአዲስ ኪዳን ተከፍሎ 81 መጻሕፍት ያሉት ሲሆን በአንዳንድ እምነቶች ደግሞ 66 ክፍል ብቻ ነው አሉት ብለው ያምናሉ። ከነዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍትም ጋራ የመጻሕፍት ቁጥር 81 ነው። ዝርዝሩን እንመጣበታለን። መጽሐፍ ቅዱስ ከመቶ 25% የአምላክ ንግግር፣ ከመቶ 25 % የነብያት ንግግር እና ከመቶ 50 % የታሪክ ጽሐፍያን ንግግር ይዟል።

በዚህ ምህዋር እና ዐውድ ላይ “ቀኖና” ስንል የዶግማ ተቃራኒ የሆነውን የሚለወጠው ሕግ ወይም ሥርዓት ሳይሆን የቅዱሳን መጽሐፍትን “መለኪያ” ታሳቢና ዋቢ ያደረገ ነው። “ቀኖና” የሚለው ቃል የአማርኛችን ቃል “ካኑን” κανών ከሚል ግሪክ ቃል የተገኘ ነው፤ ይህም ቃል “ካና” κάννα ማለት “አሰመረ” “ለካ” ከሚል የኮይኔ ግሪክ ሥርወ-ቃል የተገኘ ሲሆን “ልኬት” ማለት ነው። አይሁዳውን በ 90 ድህረ-ልደት”AD” በጀሚኒያ ጉባኤ እንዲሁ ክርስቲያኖች በ 387 ድህረ-ልደት”AD” በካርቴጅ ጉባኤ በመጨመርና በመቀነስ ቀኖና እያሉ ሲያስወጡና ሲያስገቡ ነበር፤ በተለይ የካርቴጅ ጉባኤ መጽሐፍቶችን በሁለት ከፍለው ብሉይ እና አዲስ ብለው አስቀምጠውታል፤ እስቲ ይህንን ነጥብ በነጥብ እንመልከት፦

ነጥብ አንድ “ብሉይ ኪዳን” ብሉይ ኪዳን ላይ ስላሉት መጽሐፍት የተለያዩ አንጃዎች አንድ አቋም የላቸውም፤ እነርሱን በተናጥን እስቲ እንይ፦

A. “የፕሮቴስታንት ቀኖና” ፕሮቴስታንት የሚቀበለው ሁሉም ጋር ተቀባይነት ያለው አቆጣጠር የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት 39 ናቸው፤ እነርሱም፦ 1. ኦሪት ዘፍጥረት 2. ኦሪት ዘጸአት 3 ኦሪት ዘኁልቁ 4. ኦሪት ዘሌዋውያን 5. ኦሪት ዘዳግም 6. መጽሐፈ ኢያሱ 7. መጽሐፈ መሳፍንት 8. መጽሐፈ ሩት 9. መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 10. መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ 11. መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ 12. መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ 13. ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 14. ዜና መዋዕል ካልዕ 15. መጽሐፈ ዕዝራ 16. መጽሐፈ ነህምያ 17. መጽሐፈ አስቴር 18. መጽሐፈ ኢዮብ 19. መዝሙረ ዳዊት 20. መጽሐፈ ምሳሌ 21. መጽሐፈ መክብብ 22. መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን 23. ትንቢተ ኢሳይያስ 24. ትንቢተ ኤርምያስ 25. ሰቆቃው ኤርምያስ 26. ትንቢተ ሕዝቅኤል 27. ትንቢተ ዳንኤል 28. ትንቢተ ሆሴዕ 29. ትንቢተ አሞጽ 30. ትንቢተ ሚክያስ 31. ትንቢተ ኢዮኤል 32. ትንቢተ አብድዩ 33. ትንቢተ ዮናስ 34. ትንቢተ ናሆም 35. ትንቢተ ዕንባቆም 36. ትንቢተ ሶፎንያስ 37. ትንቢተ ሐጌ 38. ትንቢተ ዘካርያስ 39. ትንቢተ ሚልክያስ ናቸው።

B. “የአይሁዳውያን ቀኖና” 39 መጽሐፍት አይሁዳውያን እንደጎሮሳውያን አቆጣጠር በ 90 ድህረ-ልደት”AD” በጀሚኒያ 24 የቀኖና መጽሐፍት አርገዋቸዋል፤ አቆጣጠራቸው ግን ይለያል፦ 1. መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ እና መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ አንድ መጽሐፍ ሻሙኤል ብለው፣ 2. መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ እና መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ አንድ መጽሐፍ መላክሂም ብለው፣ 3. ዜና መዋዕል ቀዳማዊ እና ዜና መዋዕል ካልዕ አንድ መጽሐፍ ሃያሚን ብለው፣ 4. መጽሐፈ ዕዝራ እና መጽሐፈ ነህምያ አንድ መጽሐፍ አዝራ ብለው፣ 5. ከሆሴዕ እስከ ሚልኪያስ ያሉት 12 መጽሐፍት አንድ መጽሐፍ ትሬአሳር ብለው ይቆጥሩታል።

ከሆሴዕ እስከ ሚልኪያስ ያሉት በአንድ የተጣፉትን 11 መጽሐፍት እና የተጣፉትን 4 መጽሐፍት ስንደምር 15 ይሆናል፤ 15+24= 39 መጽሐፍት ይሆናሉ። አይሁዳውያን መጽሐፍቶቻቸውን “ታንካህ” תַּנַ”ךְ, ሲሉት የሶስቱ መጽሐፍት መነሻ ላይ ያሉት ቃላት መሰረት አርገው ነው፤ እነዚህም “ታ” תַּ ቶራህ፣ “ና” נַ ነቢኢም፣ “ካ” ךְ ኬቱዊም ናቸው። “ቶራህ” תּוֹרָה ማለት “ኦሪት” “ሕግ” “መርሕ” ማለት ነው፣ ከዘፍጥረት እስከ ዘዳግም ያሉትን ለማመልከት ይጠቀሙብታል። “ነቢኢም” נְבִיאִים ማለት “ነቢያት” ማለት ሲሆን የኢሳያስ ትንቢት፣ የኤርሚያስ ትንቢት፣ የህዝቅኤል ትንቢት ወዘተ ለማመልከት ይጠቀሙብታል። “ኬቱዊም” כְּתוּבִים ማለት “መጻሕፍት” ማለት ሲሆን የኢዮብ መጽሐፍ፣ የመዝሙር መጽሐፍ፣ የምሳሌ መጽሐፍ፣ የመክብብ መጽሐፍ፣ የመኃልየ መኃልይ መጽሐፍ ወዘተ ለማመልከት ይጠቀሙብታል።

C. “የካቶሊክ ቀኖና” የሮማ ካቶሊክ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 46 ናቸው፤ ካቶሊክ በ 39 ላይ እራሳቸውን የቻሉ 7 ጭማሬ መጽሐፍት ሲኖራቸው እነዚህ ጭማሬ፦ 1. መጽሐፈ ጦቢት፣ 2. መጽሐፈ ዮዲት፣ 3. መጽሐፈ ጥበብ፣ 4. መጽሐፈ ሲራክ፣ 5. መጽሐፈ ባሮክ፣ 6. መጽሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ 7. መጽሐፈ መቃብያን ካልዕ ናቸው።

D. “የኦርቶዶክስ ቀኖና” የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 46 ናቸው፤ የብሉይ ኪዳን መደበኛ የቀኖና መጽሐፍት 39 ሲሆኑ ተጨማሪ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 18 ናቸው፤ ነገር ግን አቆጣረራቸው ልክ እንደ አይሁድ ይለያል። እራሳቸውን የቻሉ 10 ጭማሬ መጽሐፍት ሲኖራቸው እነዚህ ጭማሬ አቆጣጠራቸው፦ 1. መጽሐፈ ሄኖክ፣ 2. መጽሐፈ ኩፋሌ(ጁብሊይ)፣ 3. መጽሐፈ ጦቢት፣ 4. መጽሐፈ ዮዲት፣ 5. መጽሐፈ ተግሣጽ፣ 6. መጽሐፈ ጥበብ፣ 7. መጽሐፈ ሲራክ 8. መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ቀዳማይ እና መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ካልዕ፣ 9. መጽሐፈ መቃብያን ቀዳማይ እና መጽሐፈ መቃብያን ካልዕ፣ 10. መጽሐፈ መቃብያን ሣልስ ናቸው።

ነባር መጽሐፍት ላይ በመቀነስ ተጨፍልቀው የሚቆጠሩ 2 መጽሐፍት ናቸው፤ እነርሱም፦ 11. መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማይ እና መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ ናቸው፣ 12. መጽሐፈ ዕዝራ ቀዳማይ እና መጽሐፈ ዕዝራ ካልዕ(ነህምያ) ናቸው።

ከነባር መጽሐፍት ጋር ተደምረው የሚቆጠሩ ደግሞ 8 መጽሐፍት ናቸው፤ እነርሱም፦ 13. ከትንቢተ ኢሳይያስ ጋር የሚቆጠረው ጸሎተ ምናሴ ነው። 14. ከትንቢተ ኤርምያስ ጋር የሚቆጠሩ፦ ሰቆቃወ ኤርምያስ፣ ተረፈ ኤርምያስ፣ መጽሐፈ ባሮክ፣ ተረፈ ባሮክ ናቸው። 15. ከትንቢተ ዳንኤል ጋር የሚቆጠሩ መጽሐፈ ሶስና፣ ጸሎተ ሠለስቱ ደቂቅ እና ተረፈ ዳንኤል ናቸው።

ከ 39 ላይ 8 መጽሐፍት፦ ሳሙኤል ቀዳማይ፣ ሳሙኤል ካልዕ፣ መጽሐፈ ዕዝራ፣ መጽሐፈ ነህምያ፣ ትንቢተ ኢሳይያስ፣ ትንቢተ ኤርሚያስ፣ ሰቆቃው ኤርሚያስ እና ትንቢተ ዳንኤል ሲቀነሱ 31 መጽሐፍት ይሆናሉ። 31+15= 46 ይሆናል።

F. “የሰፕቱአጀንት ቀኖና” የሰፕቱአጀንት የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 56 ናቸው፤ የሰፕቱአጀንት”LXX” በ 39 ላይ እራሳቸውን የቻሉ 17 ጭማሬ መጽሐፍት ሲኖራቸው እነዚህ ጭማሬ፦ 1. መጽሐፈ ጦቢት፣ 2. መጽሐፈ ዮዲት፣ 3. መጽሐፈ ጥበብ፣ 4. መጽሐፈ ሲራክ፣ 5. መጽሐፈ ባሮክ፣ 6. ተረፈ ኤርምያስ፣ 7. ጸሎተ ሠለስቱ ደቂቅ፣ 8. መጽሐፈ ሶስና፣ 9. ቤልና ድራጎን፣ 10. ጸሎተ ምናሴ፣ 11.1ኛ መቃብያን፣ 12. 2ኛ መቃብያን፣ 13. 3ኛ መቃብያን፣ 14. 4ኛ. መቃብያን፣ 15. ዕዝራ ሱቱኤል፣ 16. የአዛርያ ጸሎት፣ 17. መዝሙር 151 ናቸው።

G. “የቩልጌት ቀኖና” ጄሮም በ 382 ድህረ-ልደት በላቲን ቩልጌት ባዘጋጀው ደግሞ የመጽሐፍት ቀኖና 45 ናቸው፤ የቩልጌት በ 39 ላይ እራሳቸውን የቻሉ 6 ጭማሬ መጽሐፍት ሲኖራቸው እነዚህ ጭማሬ፦ 1. መጽሐፈ ጦቢት፣ 2. መጽሐፈ ዮዲት፣ 3.1ኛ መቃብያን፣ 4. 2ኛ መቃብያን፣ 5. መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ቀዳማይ፣ 6. መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ካልዕ

የመጽሐፍ ቅዱስ ልዩ ባህርያት

መጽሐፍ ቅዱስ የስነምግባር ጉዳዮችን በሚመለከት መመሪያ የሚሰጥ ከመሆኑም ሌላ እንደ ወንጀል፣ ረሃብና የአካባቢ መበከል ያሉት ችግሮች ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መፍትሔ የሚያገኙበትን መንገድ ይገልጻል። ችግሩ ግን፣ መጽሐፍ ቅዱስ እነዚህን ጉዳዮች አስመልክቶ የሚናገረውን ነገር ብዙ ሰዎች በቁም ነገር መመልከት ትተዋል። ከዚህ ቀደም ይህ መጽሐፍ ቢያንስ በምዕራቡ ዓለም እንኳ ትልቅ ተሰሚነት ነበረው። መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው በሰዎች አማካኝነት ቢሆንም እንኳ ቀደም ባሉት ጊዜያት በሕዝበ ክርስትና ውስጥ የነበሩት አብዛኞቹ ሰዎች የአምላክ ቃል መሆኑንና መልእክቱም አምላክ በመንፈስ አነሳሽነት ያስጻፈው እንደሆነ ያምኑ ነበር።

ይሁን እንጂ ዛሬ እያንዳንዱን ነገር መጠራጠር የተለመደ ነገር ሆኗል። ሰዎች ባህላቸውን፣ የተለያዩ ጽንሰ ሐሳቦችን፣ የስነምግባር ደንቦችንና የአምላክን መኖር እንኳ ሳይቀር የጠራጠራሉ። በተለይ የመጽሐፍ ቅዱስን ጠቃሚነት በተመለከተ ጥርጣሬ ገብቷቸዋል። አብዛኞቹ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስን ጊዜ ያለፈበትና አላስፈላጊ እንደሆነ አድርገው የሚያዩት ይመስላል። ከዘመናችን ምሁራን መካከል መጽሐፍ ቅዱስን እንደ አምላክ ቃል አድርገው የሚመለከቱት በጣም ጥቂት ናቸው። እንዲያውም አብዛኞቹ ሰዎች ከምሁሩ ጄምስ ባር አባባል ጋር ይስማማሉ፡- "ስለ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ልማዶች ያለኝ አመለካከት የሰው ልጅ የፈጠራ ውጤት ናቸው የሚል ነው። የሰው ልጅ የራሱን እምነት ያሰፈረበት መጽሐፍ ነው።"[1]

ይህ አመለካከት ወደ አንድ ነጥብ ያመራል፦ መጽሐፍ ቅዱስ ሰዎች የጻፉት ተራ መጽሐፍ ከሆነ ለሰው ልጅ ችግሮች ምንም ዓይነት ግልጽ የሆነ መልስ አይገኝም ማለት ነው። የሰው ልጆች በገዛ እጃቸው በሚያመጡት ጣጣ ከህልውና ውጭ እንዳይሆኑ ወይም በኑክሊየር ጦርነት እንዳያልቁ አቅማቸው የፈቀደውን ያህል በጭፍን መዳከር ይኖርባቸዋል ማለት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ የአምላክ ቃል ከሆነ ግን ይህን አስቸጋሪ ጊዜ ለማለፍ የሚያስፈልገን ዋነኛው ነገር እርሱ ይሆናል።

የታሪክ መዝገቦች ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላሉ?

በብዛት በመሸጥ አቻ ያልተገኘለት

መጽሐፍ ቅዱስ በብዛት ታትሞ በመሸጥና በሰፊው በመሰራጨት ረገድ በሰው ዘር ታሪክ ውስጥ ቀዳሚውን ስፍራ ይዟል። ጊነስ ቡክ ኦቭ ወርልድ ሬኮርድስ የተባለው መጽሐፍ በ1988 እትሙ እንደገለጸው ከ1815 እስከ 1975 ባሉት ዓመታት ውስጥ ብቻ ወደ 2.5 ቢልዮን የሚገመቱ ቅጂዎች ታትመዋል። ይህ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ነው። የመጽሐፍ ቅዱስን ያህል ሊሰራጭ ይቅርና ወደዚያ ቁጥር የተጠጋ አንድም መጽሐፍ በታሪክ አልታየም።

ከዚህም በተጨማሪ የመጽሐፍ ቅዱስን ያህል በብዙ ቋንቋዎች የተተረጎመ መጽሐፍ አይገኝም። ዛሬ መጽሐፍ ቅዱስ ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል ከ1800 በሚበልጡ የተለያዩ ቋንቋዎች ይገኛል። በኢትዮጵያ እንኳን በአማርኛትግሪኛኦሮምኛወላይትኛጉራግኛና ሌሎች ቋንቋዎች መጽሐፍ ቅዱስ በሙሉም ሆነ በከፊል ተተርጎሞ ይገናል። በአጠቃላይ ዛሬ 98 በመቶ ገደማ የሚሆነው የምድራችን ነዋሪ መጽሐፍ ቅዱስን በቋንቋው ማግኘት ይችላል።

ተደማጭነት ያለው መጽሐፍ

ዘ ኒው ኢንሳይክለፒዲያ ብሪታኒካ መጽሐፍ ቅዱስን "በታሪክ ዘመናት ከታዩት ጽሑፎች ሁሉ ይበልጥ ተደማጭነት ያለው የመጻህፍት ስብስብ" ሲል ጠርቶታል።[2] የ19ኛው ጀርመናዊ ባለቅኔ ሄንሪክ ሃይነ እንዲህ ብለዋል፦ "ይህን ሁሉ ማስተዋል ያገኘሁት ከአንድ መጽሐፍ ነው። . . . መጽሐፍ ቅዱስን በማንበብ። ቅዱስ መጽሐፍ መባሉ ይገባዋል። አምላኩን ያጣ ሰው ካለ በዚህ መጽሐፍ አማካኝነት ሊያገኘው ይችላል።"[3] በዚሁ መቶ ዘመን የኖረውና የጸረ-ባርነት እንቅስቃሴ አራማጅ የነበረው ዊልያም ኤች ሴዋርድ እንዲህ ብሏል፦ "የሰው ልጅ የመሻሻል ተስፋ የተመካው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በሚሄደው የመጽሐፍ ቅዱስ ተደማጭነት ላይ ነው።"[4]

ዩናይትድ ስቴትስ 16ኛ ፕሬዚዳንት የነበሩት አብርሃም ሊንከን መጽሐፍ ቅዱስን በሚመለከት እንዲህ ብለዋል፦ "አምላክ ለሰው ልጆች ከሰጠው ስጦታ ሁሉ የላቀ ስጦታ ነው። . . . መጽሐፍ ቅዱስ ባይኖር ኖሮ መልካሙንና ክፉውን ለይተን ማወቅ ባልቻልን ነበር።"[5]ብሪታንያው የህግ ሰው ሰር ዊልያም ብላክስተን "ሁሉም ሰብዓዊ ሕጎች የተመሰረቱት በእነዚህ ሁለት ሕጎች ማለትም በተፈጥሮ ሕግና አምላክ ለሰው ልጆች በሰጠው ሕግ [በመጽሐፍ ቅዱስ] ላይ ነው፤ እንግዲያው ሰብዓዊ ሕጎች ከእነዚህ ሕጎች ጋር እንዲጋጩ ማድረግ አይገባም ማለት ነው።"[6] ብለው ሲናገሩ መጽሐፍ ቅዱስ ምን ያህል ተደማጭነት እንዳለው ጎላ አድርገው መግለጻቸው ነበር።

የተጠላና የተወደደ

በአንጻሩ ደግሞ በታሪክ ዘመናት ሁሉ የመጽሐፍ ቅዱስን ያህል የከረረ ተቃውሞ የገጠመው መጽሐፍ የለም። መጽሐፍ ቅዱስ ከመካከለኛው ዘመን አንስቶ እስከ 20ኛው መቶ ዘመን ድረስ በአደባባይ ተቆልሎ እንዲቃጠል ተደርጓል። በዛሬው ዘመን እንኳ ሳይቀር መጽሐፍ ቅዱስን በማንበባቸው ወይም በማሰራጨታቸው ምክንያት የገንዘብ ቅጣት የተጣለባቸው ወይም በእስራት የተቀጡ ሰዎች አሉ። ባለፉት መቶ ዘመናት እንዲህ ያለው "ወንጀል" ብዙውን ጊዜ አሰቃቂ ለሆነ ድብደባ አልፎ ተርፎም ለሞት የሚዳርግ ነበር።

መጽሐፍ ቅዱስ በሰዎች ውስጥ ያሳደረው ፍቅር ከዚሁ ጎን ለጎን የሚታይ ነው። ብዙዎች የማያቋርጥ ስደት ቢደርስባቸውም መጽሐፍ ቅዱስን ማንበባቸውን ገፍተውበታል። ለምሳሌ ያህል በ16ኛው መቶ ዘመን የኖረውንና በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ተምሮ በካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ትልቅ ቦታ ያለው አስተማሪ የነበረውን ዊልያም ቲንደልን እንመልከት።

ቲንደል ለመጽሐፍ ቅዱስ ከፍተኛ ፍቅር ነበረው። ይሁን እንጂ በዘመኑ የነበሩት ሃይማኖታዊ ባለ ሥልጣናት መጽሐፍ ቅዱስ ሙት በነበረው በላቲን ቋንቋ ተወስኖ እንዲቀር ሽንጣቸውን ገትረው የሟገቱ ነበር። ቲንደል ግን የአገሩ ሶዎች መጽሐፍ ቅዱስን የማንበብ አጋጣሚ እንዲኖራቸው በማሰብ ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋ ለመተርጎም ቆርጦ ተነሳ። ይህ ተግባሩ ከሕጉ ጋር የሚቃረን ስለነበር ቲንደል ጥሩ የማስተማር ስራውን ትቶ መሰደድ ግድ ሆነበት። የግሪክኛ ቅዱሳን ጽሑፎችን ("አዲስ ኪዳን") እና አንዳንዶቹን የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎች ("ብሉይ ኪዳን") ወደ አገሩ ቋንቋ ተርጉሞ እስኪጨርስ ኑሮውን በስደት ለመግፋት ተገዷል። ይሁን እንጂ በመጨረሻ በመያዙና መናፍቅ ነው ተብሎ በመወንጀሉ ተሰቅሎ እንዲሞትና በድኑም በእሳት እንዲቃጠል ተደርጓል።

ቲንደል፣ መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብ ወይም ለሌሎች ሰዎች እንዲዳረስ ለማድረግ ሲሉ ብዙ መሥዋዕትነት ከከፈሉት በርካታ ሰዎች መካከል አንዱ ብቻ ነው። ከሌላው ሰው የተለየ ምንም ነገር ያልነበራቸውን ብዙ ወንዶችና ሴቶች ይህን ያህል ድፍረት እንዲኖራቸው ያነሳሳ ሌላ መጽሐፍ በታሪክ ውስጥ አልታየም። ከዚህ አንጻር መጽሐፍ ቅዱስ በእርግጥም አቻ አይገኝለትም።

ማመዛገቢያ

በ"Wikimedia Commons"
(የጋራ ፎቶዎች ምንጭ)
ስለ መጽሐፍ ቅዱስ የሚገኛኙ
ተጨማሪ ፋይሎች አሉ።
  1. ^ The Bible in the Modern World, By James Barr, 1973, p. 120
  2. ^ The New Encyclopædia Britannica, 1987, Vol. 2, p.194.
  3. ^ The Book of Books: An Introduction to Solomon Goldman, 1948, p. 219.
  4. ^ The Book of Books: An Introduction, p. 222.
  5. ^ Federal Register, Vol. 48, No. 26, February 7, 1983, p.5527
  6. ^ Chadman's Cyclopedia of Law, 1912, Vol. 1, pp. 86-91.

ውጫዊ መያያዣ