ከ«የባሕር ምድር ሥርወ መንግሥት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «'''የባሕር ምድር ሥርወ መንግሥት''' በቀድሞ ሱመር (ደቡብ መስጴጦምያ ወይም ከላውዴዎን) ከባቢ...»
 
No edit summary
መስመር፡ 35፦ መስመር፡ 35፦
አንድ ሌላ ጽላት A-117 እንደ ጽላት «ለ» ያላቸውን ስሞች ከአሦራዊ ነገሥታት ዘመናት ጋራ ለማስማማት ይሞክራል፣ ሆኖም በትክክል አልተስማሙም። ከ1675 እስከ 1561 ዓክልበ ያህል ድረስ የገዙት አሦር ነገሥታት የዘመን ባልንጀሮቻቸው ቢላቸውም፣ ይህ ልክ እንደማይሆን ሊታወቅ ይቻላል።
አንድ ሌላ ጽላት A-117 እንደ ጽላት «ለ» ያላቸውን ስሞች ከአሦራዊ ነገሥታት ዘመናት ጋራ ለማስማማት ይሞክራል፣ ሆኖም በትክክል አልተስማሙም። ከ1675 እስከ 1561 ዓክልበ ያህል ድረስ የገዙት አሦር ነገሥታት የዘመን ባልንጀሮቻቸው ቢላቸውም፣ ይህ ልክ እንደማይሆን ሊታወቅ ይቻላል።


በአንድ ሰነድ በፐሽጋልዳራመሽ ፯ኛው ዓመት ወንድሙ አዳራጋላማ ደግሞ የጋርዮሽ ንጉሥ ይባላል። ከሌላ ሰነድ አዳራጋላማ ብቻ ንጉሥ የሆነው ከፐሽጋልዳራመሽ 29ኛው አመት በኋላ ነበር። ስለዚህ ወንድሞቹ ለ22 አመት ያህል የጋርዮሽ ዘመን ስለነበራቸው፣ ብዙ የሥርወ መንግሥቱ ነገሥታት ከተከታዮቻቸው ጋራ ረጅም ጋርዮሽ ዘመናት እንዳገኙ ይቻላል።


ከዚህ በላይ ስለነዚህ ነገሥታት የምናውቀው ጥቂት ብቻ ነው።
ከዚህ በላይ ስለነዚህ ነገሥታት የምናውቀው ጥቂት ብቻ ነው።
መስመር፡ 41፦ መስመር፡ 42፦
* ዳምቂ-ኢሊሹ፦ የአሚ-ዲታና መጨረሻ አመት ስም «የዳምቂ-ኢሊሹ ኃያላት የሠሩት ግድግዳ ያፈረሰበት አመት» ተባለ። የዳምቂ-ኢሊሹ ስም የቀድሞ ኢሲን መጨረሻ ንጉስ [[ዳሚቅ-ኢሊሹ]]ን (1731-1709) ያሳስባል።
* ዳምቂ-ኢሊሹ፦ የአሚ-ዲታና መጨረሻ አመት ስም «የዳምቂ-ኢሊሹ ኃያላት የሠሩት ግድግዳ ያፈረሰበት አመት» ተባለ። የዳምቂ-ኢሊሹ ስም የቀድሞ ኢሲን መጨረሻ ንጉስ [[ዳሚቅ-ኢሊሹ]]ን (1731-1709) ያሳስባል።
* ጉልኪሻር ከባቢሎን መጨረሻ ንጉሥ ሳምሱ-ዲታና ጋር እንደ ታገለ በአንድ ታሪክ ጽላት ተቀረጸ። የብርጭቆ አሠራር የሚገልጽ አንድ ጽላት «ጉልኪሻር ዘውድ ከተጫነበት ዓመት በኋላ በሆነው ዓመት» ተጽፎ ተገኝቷል። ከብዙ መቶ ዘመናት በኋላ በነገሠው በ[[ኤንሊል-ናዲን-አፕሊ]] ዘመን (1113-1109 ዓክልበ.) በተጻፈ ሰነድ ዘንድ፣ ጉልኪሻር የመቅደስን ርስት ከ696 ዓመታት በፊት እንደ ወሰነ ይጠቅሳል፤ በውነት ግን 400 ያህል ዓመታት እንዳለፉ ይሆናል።
* ጉልኪሻር ከባቢሎን መጨረሻ ንጉሥ ሳምሱ-ዲታና ጋር እንደ ታገለ በአንድ ታሪክ ጽላት ተቀረጸ። የብርጭቆ አሠራር የሚገልጽ አንድ ጽላት «ጉልኪሻር ዘውድ ከተጫነበት ዓመት በኋላ በሆነው ዓመት» ተጽፎ ተገኝቷል። ከብዙ መቶ ዘመናት በኋላ በነገሠው በ[[ኤንሊል-ናዲን-አፕሊ]] ዘመን (1113-1109 ዓክልበ.) በተጻፈ ሰነድ ዘንድ፣ ጉልኪሻር የመቅደስን ርስት ከ696 ዓመታት በፊት እንደ ወሰነ ይጠቅሳል፤ በውነት ግን 400 ያህል ዓመታት እንዳለፉ ይሆናል።
* ፐሽጋልዳራምሽ እና አዳራጋላማ የጉልኪሻር ልጆች ይባላሉ። ብዙ ሰነዶች ከዘመኖቻቸው ተገኝተዋል። አዳራጋላማ በካሣውያንና በኤላማውያን ላይ ድል እንዳደረገ ይታወቃል።
* ፐሽጋልዳራመሽ እና አዳራጋላማ የጉልኪሻር ልጆች ይባላሉ። ብዙ ሰነዶች ከዘመኖቻቸው ተገኝተዋል። አዳራጋላማ በካሣውያንና በኤላማውያን ላይ ድል እንዳደረገ ይታወቃል።
* ኤዓ-ጋሚል በካሣውያን ንጉሥ [[ኡላም-ቡርያሽ]] በ1463 ዓክልበ. ግድም ወደ [[ኤላም]] እንደ ተባረረ ይዘገባል።
* ኤዓ-ጋሚል በካሣውያን ንጉሥ [[ኡላም-ቡርያሽ]] በ1463 ዓክልበ. ግድም ወደ [[ኤላም]] እንደ ተባረረ ይዘገባል።



እትም በ23:32, 21 ኖቬምበር 2018

የባሕር ምድር ሥርወ መንግሥት በቀድሞ ሱመር (ደቡብ መስጴጦምያ ወይም ከላውዴዎን) ከባቢሎኒያ መንግሥት ተለይቶ የተነሣ መንግሥት ነበር።


በ1645 ዓክልበ. አካባቢ የኢሲን ከንቲባ ኢሉማ-ኢሊሃሙራቢ ልጅ በባቢሎን ንጉሥ ሳምሱ-ኢሉና ላይ በዓመጽ ተነሣና ሥርወ መንግሥቱን መሠረተ። ነገሥታት ሱመራዊ ስሞች ቢወስዱም፣ ያንጊዜ መደበኛ ቋንቋ አካድኛ እንደ ሆነ ይመስላል።

በባሕር ምድር ሥርወ መንግሥት ውስጥ የሚከተሉት ነገሥታት ከአንዳንድ ዝርዝር ጽላት ታውቀዋል። አንዱም ጽላት የነገሡበት ዘመን አመታት ቁጥር ቢሰጥም፣ የነዚህ ድምር ግን 368 ዓመታት ሲሆን በእውነት የቆዩበት ዓመት ከ1645-1463 ዓክልበ ወይም 182 ዓመታት ብቻ ይመስላል።

# ጽላት ሀ[1] ጽላት ለ[2] ዘመን በጽላት ሀ ዘንድ በዘመኑ በባቢሎን የነገሱ
1 ኢሊማ ኢሉማ-ኢሊ 60 ዓመት ሳምሱ-ኢሉና (1662-1624 ዓክልበ)፣ አቢ-ኤሹሕ (`1624-1596 ዓክልበ.)
2 ኢቲሊ ኢቲ-ኢሊ-ኒቢ 56 ዓመት
3 ዳምቂሊ ዳምቂ-ኢሊሹ 36 ዓመት አሚ-ዲታና መጨረሻ ዓመት ይጠቀሳል (1559 ዓክልበ.)
4 እሽኪ እሽኪባል 15 ዓመት
5 ሹሺ (ወንድሙ) ሹሺ 24 ዓመት
6 ጉልኪ… ጉልኪሻር 55 ዓመት ሳምሱ-ዲታና (1537-1508 ዓክልበ.)
7 ፐሽጋል ፐሽጋልዳራመሽ (ልጁ) 50 ዓመት
8 ዓዳራ አዳራጋላማ (የጉልኪሻር ልጅ) 28 ዓመት ካሣውያን
9 ኤኩሩል አኩርዱዓና 26 ዓመት
10 መላማ መላምኩርኩራ 7 ዓመት
11 ኤዓጋ ኤዓ-ጋሚል 9 ዓመት በካሣውያን ንጉሥ ኡላም-ቡርያሽ በ1463 ዓክልበ. ግድም ተባረረ

አንድ ሌላ ጽላት A-117 እንደ ጽላት «ለ» ያላቸውን ስሞች ከአሦራዊ ነገሥታት ዘመናት ጋራ ለማስማማት ይሞክራል፣ ሆኖም በትክክል አልተስማሙም። ከ1675 እስከ 1561 ዓክልበ ያህል ድረስ የገዙት አሦር ነገሥታት የዘመን ባልንጀሮቻቸው ቢላቸውም፣ ይህ ልክ እንደማይሆን ሊታወቅ ይቻላል።

በአንድ ሰነድ በፐሽጋልዳራመሽ ፯ኛው ዓመት ወንድሙ አዳራጋላማ ደግሞ የጋርዮሽ ንጉሥ ይባላል። ከሌላ ሰነድ አዳራጋላማ ብቻ ንጉሥ የሆነው ከፐሽጋልዳራመሽ 29ኛው አመት በኋላ ነበር። ስለዚህ ወንድሞቹ ለ22 አመት ያህል የጋርዮሽ ዘመን ስለነበራቸው፣ ብዙ የሥርወ መንግሥቱ ነገሥታት ከተከታዮቻቸው ጋራ ረጅም ጋርዮሽ ዘመናት እንዳገኙ ይቻላል።

ከዚህ በላይ ስለነዚህ ነገሥታት የምናውቀው ጥቂት ብቻ ነው።

  • ኢሉማ-ኢሊ ሳምሱ-ኢሉናን እንሳሸነፈው ይተረካል፣ ዓመት ስሞቹም በኒፑር ተገኝተው ኒፑርን እንደ ያዘ ይታስባል። የሳምሱ-ኢሉና ተከታይ አቢ-ኤሹሕ ደግሞ ኢሉማ-ኢሊን ለማሸነፍ ሲሞክር ጠግሮስ ወንዝን ገደበ፤ ይህ ግን ስኬታም አሆነለትም።
  • ዳምቂ-ኢሊሹ፦ የአሚ-ዲታና መጨረሻ አመት ስም «የዳምቂ-ኢሊሹ ኃያላት የሠሩት ግድግዳ ያፈረሰበት አመት» ተባለ። የዳምቂ-ኢሊሹ ስም የቀድሞ ኢሲን መጨረሻ ንጉስ ዳሚቅ-ኢሊሹን (1731-1709) ያሳስባል።
  • ጉልኪሻር ከባቢሎን መጨረሻ ንጉሥ ሳምሱ-ዲታና ጋር እንደ ታገለ በአንድ ታሪክ ጽላት ተቀረጸ። የብርጭቆ አሠራር የሚገልጽ አንድ ጽላት «ጉልኪሻር ዘውድ ከተጫነበት ዓመት በኋላ በሆነው ዓመት» ተጽፎ ተገኝቷል። ከብዙ መቶ ዘመናት በኋላ በነገሠው በኤንሊል-ናዲን-አፕሊ ዘመን (1113-1109 ዓክልበ.) በተጻፈ ሰነድ ዘንድ፣ ጉልኪሻር የመቅደስን ርስት ከ696 ዓመታት በፊት እንደ ወሰነ ይጠቅሳል፤ በውነት ግን 400 ያህል ዓመታት እንዳለፉ ይሆናል።
  • ፐሽጋልዳራመሽ እና አዳራጋላማ የጉልኪሻር ልጆች ይባላሉ። ብዙ ሰነዶች ከዘመኖቻቸው ተገኝተዋል። አዳራጋላማ በካሣውያንና በኤላማውያን ላይ ድል እንዳደረገ ይታወቃል።
  • ኤዓ-ጋሚል በካሣውያን ንጉሥ ኡላም-ቡርያሽ በ1463 ዓክልበ. ግድም ወደ ኤላም እንደ ተባረረ ይዘገባል።
  1. ^ Babylonian King List A, BM 33332,
  2. ^ Babylonian King List B, BM 38122.