ከ«፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ፫» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 2፦ መስመር፡ 2፦
</span>|headerstyle=background:#BCD4E6|header16=<span style="color:#0048BA">
</span>|headerstyle=background:#BCD4E6|header16=<span style="color:#0048BA">
</span>|data2=<div class=floatleft>'''[[፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ፪|&larr; ፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ፪]]</div><div class=floatright>[[፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ፬|፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ፬ &rarr;]]'''</div>|data3=[[File:UMverso.JPG|100px|thumb|center|በ፫ኛው ክፍለ ዘመን የተጻፈ ፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ፪:፫-፲፩ ገጵ ፸፰ [[:en:Papyrus 46|በፓፒረስ ፵፭ ]]''']]<br><center> ቅዱስ ጳውሎስ</center> [[ስዕል:ቅዱስ ጳውሎስ በዕሥር ቤት.jpeg|200px|center|thumb|ቅዱስ ጳውሎስ በዕሥር ቤት መልዕክቱን ሲያስተላልፍ]]</center>|header4=አጭር መግለጫ|label5=ፀሐፊ|data5=[[ጳውሎስ]]|label6=የመጽሐፍ ዐርስት|data6=፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ|label7=የሚገኘው|data7=በአዲስ ኪዳን ፯ኛው መጽሐፍ|label8=መደብ|data8=የጳውሎስ መልዕክት}}
</span>|data2=<div class=floatleft>'''[[፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ፪|&larr; ፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ፪]]</div><div class=floatright>[[፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ፬|፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ፬ &rarr;]]'''</div>|data3=[[File:UMverso.JPG|100px|thumb|center|በ፫ኛው ክፍለ ዘመን የተጻፈ ፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ፪:፫-፲፩ ገጵ ፸፰ [[:en:Papyrus 46|በፓፒረስ ፵፭ ]]''']]<br><center> ቅዱስ ጳውሎስ</center> [[ስዕል:ቅዱስ ጳውሎስ በዕሥር ቤት.jpeg|200px|center|thumb|ቅዱስ ጳውሎስ በዕሥር ቤት መልዕክቱን ሲያስተላልፍ]]</center>|header4=አጭር መግለጫ|label5=ፀሐፊ|data5=[[ጳውሎስ]]|label6=የመጽሐፍ ዐርስት|data6=፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ|label7=የሚገኘው|data7=በአዲስ ኪዳን ፯ኛው መጽሐፍ|label8=መደብ|data8=የጳውሎስ መልዕክት}}
፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ [[አዲስ ኪዳን|በአዲስ ኪዳን]] ሁለተኛው መልዕክት ሲሆን [[ቅዱስ ጳውሎስ]] በቆሮንጦስ እያለ በ፶ ዎቹ ዓ.ም. ለቆሮንጦስ ሰዎች የጻፈው የመጀመሪያ መልዕክት ነው ። ፲፮ ምዕራፎች ይይዛል ። ይህ ፫ኛ ምዕራፍ ሲሆን ንዑስ ክፍሎች ይከፈላል ።
፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ [[አዲስ ኪዳን|በአዲስ ኪዳን]] ሁለተኛው መልዕክት ሲሆን [[ቅዱስ ጳውሎስ]] በቆሮንጦስ እያለ በ፶ ዎቹ ዓ.ም. ለቆሮንጦስ ሰዎች የጻፈው የመጀመሪያ መልዕክት ነው ። ፲፮ ምዕራፎች ይይዛል ። ይህ ፫ኛ ምዕራፍ ሲሆን በ፳፫ ንዑስ ክፍሎች ይከፈላል ።




መስመር፡ 9፦ መስመር፡ 9፦


የሐዋርያው ጳውሎስ መልዕክት ፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ምዕራፍ ፫
የሐዋርያው ጳውሎስ መልዕክት ፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ምዕራፍ ፫

== ቁጥር ፩ - ፲ ==
== ቁጥር ፩ - ፲ ==
1፤እኔም፥ወንድሞች፡ሆይ፥የሥጋ፡እንደ፡መኾናችኹ፥በክርስቶስም፡ሕፃናት፡እንደ፡መኾናችኹ፡እንጂ፡
1፤እኔም፥ወንድሞች፡ሆይ፥የሥጋ፡እንደ፡መኾናችኹ፥በክርስቶስም፡ሕፃናት፡እንደ፡መኾናችኹ፡እንጂ፡

እትም በ04:55, 2 ኦገስት 2019

፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ፫
በ፫ኛው ክፍለ ዘመን የተጻፈ ፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ፪:፫-፲፩ ገጵ ፸፰ በፓፒረስ ፵፭

ቅዱስ ጳውሎስ
ቅዱስ ጳውሎስ በዕሥር ቤት መልዕክቱን ሲያስተላልፍ
አጭር መግለጫ
ፀሐፊ ጳውሎስ
የመጽሐፍ ዐርስት ፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ
የሚገኘው በአዲስ ኪዳን ፯ኛው መጽሐፍ
መደብ የጳውሎስ መልዕክት


፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ በአዲስ ኪዳን ሁለተኛው መልዕክት ሲሆን ቅዱስ ጳውሎስ በቆሮንጦስ እያለ በ፶ ዎቹ ዓ.ም. ለቆሮንጦስ ሰዎች የጻፈው የመጀመሪያ መልዕክት ነው ። ፲፮ ምዕራፎች ይይዛል ። ይህ ፫ኛ ምዕራፍ ሲሆን በ፳፫ ንዑስ ክፍሎች ይከፈላል ።


ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንጦስ ሰዎች መልዕክት የጻፈበት ምክኒያት ብዙ ሲሆን ከብዙዎች በጥቂቱ ፣ ከመምህሮቻቸው መዐረግ ሳይደርሱ ደረስን እያሉ በብዙ ቐንቐ በሚናገሩ መምህሮቻቸው እንደነ ራሱ ፣ ጳውሎስ ፣ አጵሎስ... ላይ የሚታበዩ ስለተነሱ ለነዚህ እንደ ዘለፋ እንዲሆን ፤ በቆሮንቶስ ምዕመናን መሀከል መከፋፈላቸውን ሰምቶ ከዚህ ስህታቸው እንዲታረሙ ፤ በተጨማሪም ዓለምን ለማሳፈር እግዚአብሔር ታላቁን ሚሥጥር በዓለም በተናቁት ሰዎች እንዲገለፅ ማድረጉን ለማሳወቅ ጻፈው ።

የሐዋርያው ጳውሎስ መልዕክት ፩ኛ ወደ ቆሮንጦስ ምዕራፍ ፫

ቁጥር ፩ - ፲

1፤እኔም፥ወንድሞች፡ሆይ፥የሥጋ፡እንደ፡መኾናችኹ፥በክርስቶስም፡ሕፃናት፡እንደ፡መኾናችኹ፡እንጂ፡ መንፈሳውያን፡እንደ፡መኾናችኹ፡ልናገራችኹ፡አልቻልኹም። 2፤ገና፡ጽኑ፡መብል፡ለመብላት፡አትችሉም፡ነበርና፥ወተት፡ጋትዃችኹ፤ 3፤ገና፡ሥጋውያን፡ናችኹና፥እስከ፡አኹን፡ድረስ፡ገና፡አትችሉም።ቅናትና፡ክርክር፡ስለሚገኝባችኹ፡ ሥጋውያን፡መኾናችኹ፡አይደላችኹምን፧እንደ፡ሰው፡ልማድስ፡አትመላለሱምን፧ 4፤አንዱ፦እኔ፡የጳውሎስ፡ነኝ፥ኹለተኛውም፦እኔ፡የአጵሎስ፡ነኝ፡ቢል፡ሰዎች፡ብቻ፡መኾናችኹ፡ አይደለምን፧ 5፤አጵሎስ፡እንግዲህ፡ምንድር፡ነው፧ጳውሎስስ፡ምንድር፡ነው፧በእነርሱ፡እጅ፡ያመናችኹ፡አገልጋዮች፡ ናቸው፤ለያንዳንዳቸውም፡ጌታ፡እንደ፡ሰጣቸው፡ያገለግላሉ። 6፤እኔ፡ተከልኹ፡አጵሎስም፡አጠጣ፥ነገር፡ግን፥እግዚአብሔር፡ያሳድግ፡ነበር፤ 7፤እንግዲያስ፡የሚያሳድግ፡እግዚአብሔር፡እንጂ፡የሚተክል፡ቢኾን፡ወይም፡የሚያጠጣ፡ቢኾን፡አንዳች፡ አይደለም። 8፤የሚተክልና፡የሚያጠጣ፡አንድ፡ናቸው፥ነገር፡ግን፥እያንዳንዱ፡እንደ፡ራሱ፡ድካም፡መጠን፡የራሱን፡ ደመ፡ወዝ፡ይቀበላል። 9፤የእግዚአብሔር፡ዕርሻ፡ናችኹ፤የእግዚአብሔር፡ሕንፃ፡ናችኹ፤ከርሱ፡ጋራ፡ዐብረን፡የምንሠራ፡ነንና። 10፤የእግዚአብሔር፡ጸጋ፡እንደተሰጠኝ፡መጠን፡እንደ፡ብልኀተኛ፡የዐናጺ፡አለቃ፡መሠረትን፡ መሠረትኹ፥ሌላውም፡በላዩ፡ያንጻል። እያንዳንዱ፡ግን፡በርሱ፡ላይ፡እንዴት፡እንዲያንጽ፡ይጠንቀቅ።

ቁጥር ፲፩ - ፳፫

11፤ከተመሠረተው፡በቀር፡ማንም፡ሌላ፡መሠረት፡ሊመሠርት፡አይችልምና፥ርሱም፡ኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ነው። 12፤ማንም፡ግን፡በዚህ፡መሠረት፡ላይ፡በወርቅ፡ቢኾን፡በብርም፡በከበረ፡ድንጋይም፡በዕንጨትም፡በሣርም፡ ወይም፡በአገዳ፡ቢያንጽ፥የያንዳንዱ፡ሥራ፡ይገለጣል፤ 13፤በእሳት፡ስለሚገለጥ፡ያ፡ቀን፡ያሳያልና፥የያንዳንዱም፡ሥራ፡እንዴት፡መኾኑን፡እሳቱ፡ይፈትነዋል። 14፤ማንም፡በርሱ፡ላይ፡ያነጸው፡ሥራ፡ቢጸናለት፡ደመ፡ወዙን፡ይቀበላል፤ 15፤የማንም፡ሥራ፡የተቃጠለበት፡ቢኾን፡ይጐዳበታል፥ርሱ፡ራሱ፡ግን፡ይድናል፥ነገር፡ግን፥በእሳት፡እንደሚድን፡ይኾናል። 16፤የእግዚአብሔር፡ቤተ፡መቅደስ፡እንደ፡ኾናችኹ፡የእግዚአብሔርም፡መንፈስ፡እንዲኖርባችኹ፡አታውቁምን፧ 17፤ማንም፡የእግዚአብሔርን፡ቤተ፡መቅደስ፡ቢያፈርስ፡እግዚአብሔር፡ርሱን፡ያፈርሰዋል፤የእግዚአብሔር፡ቤተ፡ መቅደስ፡ቅዱስ፡ነውና፥ያውም፡እናንተ፡ናችኹ። 18፤ማንም፡ራሱን፡አያታል፟፤ከእናንተ፡ማንም፡በዚች፡ዓለም፡ጥበበኛ፡የኾነ፡ቢመስለው፡ጥበበኛ፡ይኾን፡ ዘንድ፡ሞኝ፡ይኹን። 19-20፤የዚች፡ዓለም፡ጥበብ፡በእግዚአብሔር፡ፊት፡ሞኝነት፡ነውና፦ርሱ፡ጥበበኛዎችን፡በተንኰላቸው፡ የሚይዝ፤ደግሞም፦ጌታ፡የጥበበኛዎችን፡ዐሳብ፡ከንቱ፡እንደ፡ኾነ፡ያውቃል፡ተብሎ፡ተጽፏልና። 21፤ስለዚህም፡ማንም፡በሰው፡አይመካ።ነገር፡ዅሉ፡የእናንተ፡ነውና፤ 22፤ጳውሎስ፡ቢኾን፡አጵሎስም፡ቢኾን፡ኬፋም፡ቢኾን፡ዓለምም፡ቢኾን፡ሕይወትም፡ቢኾን፡ሞትም፡ቢኾን፡ያለውም፡ቢኾን፡የሚመጣውም፡ቢኾን፥ 23፤ዅሉ፡የእናንተ፡ነው፥እናንተም፡የክርስቶስ፡ናችኹ፡ክርስቶስም፡የእግዚአብሔር፡ነው።