ከ«የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፫» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit |
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit |
||
መስመር፡ 1፦ | መስመር፡ 1፦ | ||
<center>{{infobox |
<center>{{infobox |
||
|abovestyle=background:#BCD4E6 |
|abovestyle=background:#BCD4E6 |
||
|above=<h1><span style=color:blue>የማርያም ቅዳሴ</span><div class= |
|above=<h1><span style=color:blue>የማርያም ቅዳሴ</span><div class=floatcenter> |
||
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1> |
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1> |
||
<p><span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span> |
<p><span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span> |
እትም በ06:33, 23 ኖቬምበር 2019
የማርያም ቅዳሴዘቅዱስ ሕርያቆስ |
---|
፲፫ ፤ በቀናች ሃይማኖት ስላረፉ ስለ ቅዱሳን ሰማዕታት ሁሉ ጳውሎስ ጢሞቴዎስ ሲላስና በርናባስ ቲቶና ፊሊሞንና ቀለምንጦስም ሰባ ሁለቱ አርድዕት አምስት መቶ ባልንጀራዎች ሃይማኖታቸው ስለ ቀና ስለ ሦስት መቶ አሥራ ስምንቱ ።
፲፬ ፤ እሊህንም ሁሉንም ለአንተ ወገን ሊሆኑ አስባቸው ፣ ብፁዕ ወቅዱስ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት አባ....
ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አባ.... አስባቸው በሕይወታቸውም ትጠብቃቸው ዘንድ ኃጢያታቸውንም ይቅር ትላቸው ዘንድ እኛንም በእነርሱ ጸሎት ትምረን ዘንድ ለዘላለሙ ።
፲፭ ፤ ጸሎተ ቡራኬ ፣ ቅዳሴ ሐዋርያት ቁ ፲ - ፳፩ ።
፲፮ ፤ የጳጳሳቱን አለቆች ጳጳሳቱንና ኤጲስ ቆጶሳቱን ቀሳውስቱንና ዲያቆናቱን የክርስቲያንንም ወገኖች ሁሉ አቤቱ ማራቸው ይቅርም በላቸው ።
፲፯ ፤ አማላጅቱ ሆይ እሊህንም ሁሉንም ከልጅሽ ዘንድ አማልጂ የጳጳሳትንና የሊቃነ ጳጳሳትን የኤጲስ ቆጶሳትን ሁሉ ነፍስ ያሳርፍ ዘንድ የቀሳውስትንና የዲያቆናትንም ዕውነተኛውን የቃል ጎዳና የሚያቀኑ ። ነገሥታትና መኳንንቱን መሳፍንቱንም በሥልጣን የሚኖሩትን ወራዙትንና ደናግልን መነኮሳትንምባለጠጋውንና ድሀውን ታላቁንና ታናሹን ባልቴቱንና አባት እናት የሞቱበትን መጻተኛውንና ችግረኛውን አስቀድሞ ከቤተክርስቲያን ማኅበር ተለይተው ያረፉትን የክርስቲያንንም ወገኖች ሁሉ ።