ከ«የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፯» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit
መስመር፡ 1፦ መስመር፡ 1፦
<center>{{infobox
<center>{{infobox
|abovestyle=background:#BCD4E6
|abovestyle=background:#BCD4E6
|above=<h1><span style=color:blue>የማርያም ቅዳሴ</span><div class=floatcenter>
|above=<h1><span style=color:blue>የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፯</span><div class=floatcenter>
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1>
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1>
<p><span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span>
<p><span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span>

እትም በ12:35, 5 ጃንዩዌሪ 2020

የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፯

ዘቅዱስ ሕርያቆስ


፴፯ ፤  ድንግል ሆይ በኃጢያት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ ።
፴፰ ፤  ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም በንጽሕና በቅድስና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ ።
፴፱ ፤  ድንግል ሆይ ምድራዊ ኅብስትን የተመገብሽ አይደለሽም ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ኅብስትን ነው እንጂ ።
፵ ፤  ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለም ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጠጥን ነው እንጂ ።
፵፩ ፤  ድንግል ሆይ ከአንቺ አስቀድሞ ከአንቺም በኋላ እንዳሉ ሴቶች እድፍ የምታውቂ አይደለሽም በንጽሕና በቅድስና ያጌጥሽ ነሽ እንጂ ።
፵፪ ፤  ድንግል ሆይ የሚያታልሉ ጎልማሶች ያረጋጉሽ አይደለሽም የሰማይ መላእክት ጎበኙሽ እንጂ ። እንደተነገረ ካህናትና የካህናት አለቆች አመሰገኑሽ እንጂ ።
፵፫ ፤  ድንግል ሆይ ለዮሴፍ የታጨሽ ለመገናኘት አይደለም ንጹሕ ሆኖ ሊጠብቅሽ ነው እንጂ ። እንዲሁ ስለሆነ ።
፵፬ ፤ እርሱ ቅሉ  እግዚአብሔር አብ ንጽሕናሽን ባየ ጊዜ ስሙ ገብርኤል የሚባል ብርሃናዊ መልአኩን ወደ አንቺ ላከ ።  መንፈስ ቅዱስ በላይሽ ይመጣል የልዑል ኃይልም ይጋርድልሻል አለሽ ።