ከ«ነነዌ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
ጥ Removing Link FA template (handled by wikidata) |
No edit summary Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ |
||
መስመር፡ 2፦ | መስመር፡ 2፦ | ||
|ስም = ነነዌ |
|ስም = ነነዌ |
||
|ኗሪ ስም = (''ናይኑዋ'') |
|ኗሪ ስም = (''ናይኑዋ'') |
||
|ስዕል = Adad gate exterior entrance |
|ስዕል = Nineveh Adad gate exterior entrance far2.JPG |
||
|caption = የታደሰው አዳድ በር ፍርስራሽ |
|caption = የታደሰው አዳድ በር ፍርስራሽ |
||
|ዘመናዊ አገር = ኢራቅ |
|ዘመናዊ አገር = ኢራቅ |
በ12:37, 14 ማርች 2020 የታተመው ያሁኑኑ እትም
ነነዌ (ናይኑዋ) | |
---|---|
የታደሰው አዳድ በር ፍርስራሽ | |
ሥፍራ | |
መንግሥት | የአሦር መንግሥት |
ዘመን | ከ2380 እስከ 620 ዓክልበ. |
ዘመናዊ አገር | ኢራቅ |
ጥንታዊ አገር | አሦር |
ነነዌ የአሦር ጥንታዊ ከተማ ነበረ። ፍርስራሹ በጤግሮስ ወንዝ ምሥራቅ ዳርቻ በሞሱል ዙሪያ አሁን አለ።
በኦሪት ዘፍጥረት 10፡11 መሠረት የሴም ልጅ አሦር ከሰናዖር ወጥቶ ነነዌንና ሌሎችን ከተሞች ሠራ። አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ግን ከፊተኛው ቁጥር ከ10፡10 በመውሰድ አድራጊው እንደ ናምሩድ ቆጥረውት፣ ናምሩድ እራሱ ወደ አሦር (ወደ ሀገሩ) ወጥቶ እኚህን ከተሞች እንደ ሠራ ይላሉ። በጥንታዊ የግሪክ ታሪክ ጸሃፊዎች ዘንድ ኒኑስ የነነዌ መስራችና የአሦር መጀመርያ ንጉስ ነበረ።
ነነዌ ከጥንት ጀምሮ ከአሹር ከተማ-አገር ይገዛ ነበር። እንደ አሹር ከ1440 እስከ 1366 ዓክልበ. ድረስ በሚታኒ ይቆጣጠር ነበር። ትልቅ ከተማ ነበረ።
በ775 ዓክልበ. አካባቢ ነቢዩ ዮናስ ወደ ነነዌ ሂዶ የአሦር ሰዎች ወደ ንሥሐ እንዳመጣቸው በመጽሐፈ ዮናስ ይገለጻል። የዮናስ መቃብር የሚባለው የተቀደሠ መስጊድ በነነዌ (የአሁኑ ሞሱል) አካባቢ ይገኝ ነበር፤ በሐምሌ 2006 ዓ.ም. የኢስላማዊ ተዋጊዎች ከ«ኢስላም ግዛት በኢራቅና ሶርያ» ወገን የዮናስን መስጊድ አፈረሱት።
በ713 ዓክልበ. ንጉሥ ሰናክሬም የአሦርን ዋና ከተማ ወደ ነነዌ መለሠው።