ከ«የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፬» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit
Added links
Tags: በንፋስ ስልክ Mobile app edit iOS app edit
መስመር፡ 2፦ መስመር፡ 2፦
|abovestyle=background:#BCD4E6
|abovestyle=background:#BCD4E6
|above=<h1><span style=color:blue>የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፬</span><div class=floatcenter>
|above=<h1><span style=color:blue>የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፬</span><div class=floatcenter>
|image=[[ስዕል:ፀሎተ ሐሙስ.jpeg]]
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1>
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1>
<p><span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span>
<p><span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span>

እትም በ04:15, 12 ኦክቶበር 2021

የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፬

ዘቅዱስ ሕርያቆስ


፹፱ ፤ ቀሳውስት እጆቻችሁን አንሱ ።
፺ ፤ ያን ጊዜ ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳት ብፁዐት በሚሆኑ እድፍ በሌለባቸው እጆቹ ኅብቱን አነሣ ።
፺፩ ፤ እናምናለን ይህ እርሱ እንደሆነ በውነት እናምናለን ።
፺፪ ፤ ወደ ሰማይ ወደ አባቱ ቀና ብሎ አየ የወለደውንም ማለደ ። ደቀ መዛሙርቱንም ከክፉ ሁሉ ይጠብቃቸው ዘንድ አደራ አስጠበቀ ። ብሩክ ሲሆን ባረከ ። ቅዱስ ሲሆን ቆረሰ ።
፺፫ ፤ ከዚያም በኋላ ኅብስቱን ሳይለየው ከአምስት ላይ ያንቃው ።
፺፬ ፤ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው ። ይህ ኅብስት "እማሬ" ለዓለም ሁሉ ቤዛ ሊሆን ስለናንተ የሚሰጥ ሥጋዬ ነው አላቸው ።
፺፭ ፤ አሜን አሜን አሜን እናምናለን እንታመናለንም ጌታችን አምላካችን ሆይ እናመሰግንሃለን ይህ እርሱ እንደሆነ በእውነት እናምናለን ።
፺፮ ፤ እንዲሁም ጽዋውን ሦስት ጊዜ ይባርክ ከተመገቡ በኋላ አመለከተ ። ይህ ጽዋ "እማሬ"ስለናንተ ጦር የማያፈሰው ደሜ ነው ንሡ ጠጡ አለ ።
፺፯ ፤ ጽዋውን በቀኝ እጁ በአራቱ መዐዘን ይወዝውዘው ።
፺፰ ፤ አሜን አሜን አሜን እናምናለን ። እንታመናለን ።
፺፱ ፤ ይህን በምታደርጉበት ጊዜ የሞቱን መታሰቢያ ታደርጋላቹህ ። የትንሣኤውንም መታሰቢያ ትናገራላቹህ ።