ከ«የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፯» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit |
Added links Tags: በንፋስ ስልክ Mobile app edit iOS app edit |
||
መስመር፡ 2፦ | መስመር፡ 2፦ | ||
|abovestyle=background:#BCD4E6 |
|abovestyle=background:#BCD4E6 |
||
|above=<h1><span style=color:blue>የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፯</span><div class=floatcenter> |
|above=<h1><span style=color:blue>የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፯</span><div class=floatcenter> |
||
|image=[[ስዕል:ፀሎተ ሐሙስ.jpeg]] |
|||
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1> |
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1> |
||
<p><span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span> |
<p><span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span> |
እትም በ04:16, 12 ኦክቶበር 2021
የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፯ | |
---|---|
ዘቅዱስ ሕርያቆስ |
፻፴፬ ፤ ጸልዩ አቡነ ዘበሰማያት ።
፻፴፭ ፤ እንግዲህ እስከ ደኃሪት እስትንፋስ (ዕለተ ሞት) ድረስ ይህን ቃል እንስማ በምንከሰስበት ገንዘብ በሚፈረድብንና ይቅር በሚለን ገንዘብ ።
፻፴፮ ፤ ወልድ ለመፍረድና ይቅር ለማለት ከሰማየ ሰማያት እንደመጣ እንደዚሁም ይህ ኅብስት ከሳሽ ነው ፈራጅም ነው ይቅር ባይም ነው ።
፻፴፯ ፤ ከዚህ ከሚያስደነግጥ ቃል የተነሣ ነፍስ ትፍራ ሕዋስ ይንቀጥቀጥ በውስጥ ያለ ነፍስ የልብ ደጅም ይሰበር ።
፻፴፰ ፤ ይህን መለኮታዊ ኅብስት እንሆ ተቆረሰ ። ይህ ማኅየዊ ጽዋ እንሆ ተዘጋጀ ። የሚቀበል ይምጣ ። አስቀድሞ ራሳቹህን መርምሩ ሰውነታቹህንም አንጹ ።
፻፴፱ ፤ ንጹሕ ያልሆነ ሰው ቢኖር ይወገድ በኃጢአት የወደቀ ሰው ቢኖር አይርሳ የማይረሳ ነውና ።
፻፵ ፤ ይህን ቁርባን የሚያቃልል ሰው ቢኖር አይቅረብ ይከልከል እንጂ ይህ ኅብስት እንደምታዩት እንደ ምድራዊ ኅብስት ብላሽ አይደለም ። እሳት ነው እንጂ ።
፻፵፩ ፤ ይህን ኅብስት የሚጎርስ ምን አፍ ነው ይህን
ኅብስት የሚያላምጥ ምን ጥርስ ነው ይህን ኅብስት የሚችል ምን ሆድ ነው ።?
፻፵፪ ፤ አሁንም አምላካችን ሆይእንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደ ኃጢአታችን አይደለም እንበል ።
፻፵፫ ፤ አምላካችን ሆይ እንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደ ኃጢአታችንም አይደለም (፫ ጊዜ) ።
፻፵፬ ፤ ከዚህም በኋላ የመድኃኔ ዓለም የመላዕክት ሠራዊት በመድኃኔ ዓለም ፊት ይቆማሉ ።
መድኃኔ ዓለምን ያመሰግኑታል
የመድኃኔ ዓለም ሥጋውና ደሙን ።
ወደ መድኃኔ ዓለም ፊት እንቅረብ እርሱንም በማመን ለክርስቶስ እንገዛለን ።