ከ«የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፫» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
Added links
Tags: በንፋስ ስልክ Mobile app edit iOS app edit
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit
መስመር፡ 4፦ መስመር፡ 4፦
|image=[[ስዕል:ፀሎተ ሐሙስ.jpeg]]
|image=[[ስዕል:ፀሎተ ሐሙስ.jpeg]]
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1>
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1>
<p><span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span>
|data1=<span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span>
|width=300px
|width=300px
}}</center>
}}</center>

እትም በ06:57, 12 ኦክቶበር 2021

የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፫

ዘቅዱስ ሕርያቆስ

፲፫ ፤ በቀናች ሃይማኖት ስላረፉ ስለ ቅዱሳን ሰማዕታት ሁሉ ጳውሎስ ጢሞቴዎስ ሲላስና በርናባስ ቲቶና ፊሊሞንና ቀለምንጦስም ሰባ ሁለቱ አርድዕት አምስት መቶ ባልንጀራዎች ሃይማኖታቸው ስለ ቀና ስለ ሦስት መቶ አሥራ ስምንቱ ።
፲፬ ፤ እሊህንም ሁሉንም ለአንተ ወገን ሊሆኑ አስባቸው ፣ ብፁዕ ወቅዱስ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት አባ.... ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አባ.... አስባቸው በሕይወታቸውም ትጠብቃቸው ዘንድ ኃጢያታቸውንም ይቅር ትላቸው ዘንድ እኛንም በእነርሱ ጸሎት ትምረን ዘንድ ለዘላለሙ ።
፲፭ ፤ ጸሎተ ቡራኬ ፣ ቅዳሴ ሐዋርያት ቁ ፲ - ፳፩ ።
፲፮ ፤ የጳጳሳቱን አለቆች ጳጳሳቱንና ኤጲስ ቆጶሳቱን ቀሳውስቱንና ዲያቆናቱን የክርስቲያንንም ወገኖች ሁሉ አቤቱ ማራቸው ይቅርም በላቸው ።
፲፯ ፤ አማላጅቱ ሆይ እሊህንም ሁሉንም ከልጅሽ ዘንድ አማልጂ የጳጳሳትንና የሊቃነ ጳጳሳትን የኤጲስ ቆጶሳትን ሁሉ ነፍስ ያሳርፍ ዘንድ የቀሳውስትንና የዲያቆናትንም ዕውነተኛውን የቃል ጎዳና የሚያቀኑ ። ነገሥታትና መኳንንቱን መሳፍንቱንም በሥልጣን የሚኖሩትን ወራዙትንና ደናግልን መነኮሳትንምባለጠጋውንና ድሀውን ታላቁንና ታናሹን ባልቴቱንና አባት እናት የሞቱበትን መጻተኛውንና ችግረኛውን አስቀድሞ ከቤተክርስቲያን ማኅበር ተለይተው ያረፉትን የክርስቲያንንም ወገኖች ሁሉ ።