ከ«የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፭» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Added links Tags: በንፋስ ስልክ Mobile app edit iOS app edit |
No edit summary Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit |
||
መስመር፡ 4፦ | መስመር፡ 4፦ | ||
|image=[[ስዕል:ፀሎተ ሐሙስ.jpeg]] |
|image=[[ስዕል:ፀሎተ ሐሙስ.jpeg]] |
||
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1> |
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1> |
||
|data1=<span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span> |
|||
}}</center> |
}}</center> |
||
<br>፳፬ ፤ እናስተውል ። |
<br>፳፬ ፤ እናስተውል ። |
እትም በ07:00, 12 ኦክቶበር 2021
የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፭ | |
---|---|
ዘቅዱስ ሕርያቆስ |
፳፬ ፤ እናስተውል ።
፳፭ ፤ አንቺን የወደደ እግዚአብሔር አብ ቅዱስነው ፣ በመኀፀንሽ ያደረ ወልድ ዋህድም ቅዱስ ነው ፣ ያጸናሽም የጽድቅ መንፈስ ጰራቅሊጦስ ቅዱስ ነው ።
፳፮ ፤ ተሰጥዎውን መልሱ ።
፳፯ ፤ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ፍጹም አሸናፊ እግዚአብሔር የጌትነትህ ምስጋና በሰማይና በምድር የመላ ነው ።
፳፰ ፤ ምስጋናን የተመላሽ ድንግል ሆይ በማንና በማንስ ምሳሌ እንመስልሻለን ። አማኑኤልየማይተረጎም የሥጋን ልብስነት ከአንቺ የለበሳት መሣሪያ ነሽ ። ዝሐውን ከአዳም ጥንተ ሥጋ አደረገ ማጉም ያንቺ ሥጋ ነው ። መወርወሪያውም ቃል እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ። መሕኑም ከልዕልና የወረደ የልዑል እግዚአብሔር አምሳል ነው ሠሪውም መንፈስ ቅዱስ ነው ።
፳፱ ፤ ወዮ ይህ ነገር ዕፁብ ድንቅ ነው የቀደሙ አባቶች ከሞት ወደ ሕይወት የተሸጋገሩባሽ ድልድይ ሆይ ከምድር እስከ ሰማይ የምትደርሽ መሰላል ሆይ የፍጥረት ሁሉ መጀመሪያ ባንቺ ታደሰ ።
፴ ፤ ከገነት በተሰደደ ጊዜ ለአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ ። በግፍ የተገደለ የአቤል የውሃቱ አንቺ ነሽ ። የሴት ቸርነት አንቺ ነሽ ። የሄኖክም ሥራዎቹ ከክፉ ጥፋት የዳነባት ። የኖህ መርከብ ፣ የሴም ቡራኬ ዕድል ፈንታውም አንቺ ነሽ ።
፴፩ ፤ የአብርሃም እንግድነት የያዕቆብ መሰላል አንቺ ነሽ ። ዮሴፍን የምታረጋጊው አንቺ ነሽ ።