ከ«የማርያም ቅዳሴ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit |
No edit summary Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit |
||
መስመር፡ 11፦ | መስመር፡ 11፦ | ||
|data2=ግብፅ (ብኅንሳ) |
|data2=ግብፅ (ብኅንሳ) |
||
|label3=የተወለደበት ዘመን |
|label3=የተወለደበት ዘመን |
||
|data3=ዘመነ ሊቃውንት |
|data3=ዘመነ ሊቃውንት (ከ፫፻ እስከ፬፻ ዓ.ም) ማለት ነው |
||
}}</center> |
}}</center> |
||
[[File:Livre.png|75px]] |
[[File:Livre.png|75px]] |
እትም በ07:16, 12 ኦክቶበር 2021
አባ ሕርያቆስ ኤጲስ ቆጶስ አምላክን ስለ ወለደች ስለ እመቤታችን ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ የደረሰው የቁርባን ምስጋና ይህ ነው ። ልመናዋ በረከትዋ ከሁላችን ጋራ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን ።
የማርያም ቅዳሴዘቅዱስ ሕርያቆስ | |
---|---|
የቅዱስ ሕርያቆስ የንግሥ ቀን | ጥቅምት ፪ (ያረፈበት) |
የትውልድ ሀገሩ | ግብፅ (ብኅንሳ) |
የተወለደበት ዘመን | ዘመነ ሊቃውንት (ከ፫፻ እስከ፬፻ ዓ.ም) ማለት ነው |
፩ ፤ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን ። ከመንፈስህ ጋር አምላካችንን አመስግኑት ። እውነት ነው ይገባዋል ። ልቦናችሁን ከፍ ከፍ አድርጉ ። በአምላካችን በእግዚአብሔር ዘንድ አለን ።
፪ ፤ ልቦናዬ በጎ ነገርን አወጣ ።ልቦናዬ በጎ ነገርን አወጣ ። ልቦናዬ በጎ ነገርን አወጣ ።
፫ ፤ እኔም የማርያምን ቅዳሴ እናገራለሁ ። በማብዛት አይደለም በማሳነስ ነው እንጂ ። እኔም የድንግልን ውዳሴ እናገራለሁ ። መዘንጋት ባለበት ቃል በማስረዘም አይደለም ። በማሳጠር ነው እንጂ እኔም የድንግልን ገናንነትዋን እናገራለሁ ።
፬ ፤ ዛሬ በዚች ቀን በፍቅርና በትሕትና ግሩም በሚሆን ምሥጢር ፊት እቆማለሁ ። በዚህ ማዕድና ቁርባን ፊት ።
፭ ፤ መንፈሳቸውን ያረከሱ ሰዎች ከርሱ ሊቀምሱ የማይቻላቸው በእውነት ቁርባን ነው ። በበግ በጊደርና በላም ደም እንደ ነበረው እንደ ቀደሙት አባቶች መሥዋዕት አይደለም እሳት ነው እንጂ ።
፮ ፤ ፈቃዱን ለሚሠሩ ልቦናቸውን ላቀኑ ሰዎች የሚያድን እሳት ነው ። ስሙን ለሚክዱ ለዓመፀኞች ሰዎች የሚበላ እሳት ነው ።
ገፅ ፩