ከ«ቅዱስ መርቆሬዎስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
Fixed grammar
Tags: በንፋስ ስልክ Mobile app edit iOS app edit
Added content
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 33፦ መስመር፡ 33፦
ይህ ታማኝ ምስክርነት የሰጠ ሰማዕት ወላጆቹ ጣዖት የሚያመልኩ አረማውያን ነበሩ።ከጊዜ ወደ ጊዜ የክርስትና እምነት እየተስፋፋ ስለ ሄደ ቤተሰቦቹም ክርስቲያኖች ሆነዋል።
ይህ ታማኝ ምስክርነት የሰጠ ሰማዕት ወላጆቹ ጣዖት የሚያመልኩ አረማውያን ነበሩ።ከጊዜ ወደ ጊዜ የክርስትና እምነት እየተስፋፋ ስለ ሄደ ቤተሰቦቹም ክርስቲያኖች ሆነዋል።
እሱም ካደገ በኋላ ተምሮና አምኖ ተጠመቀ ስመ ጥምቀቱም መርቆሬዎስ ተባለ ።
እሱም ካደገ በኋላ ተምሮና አምኖ ተጠመቀ ስመ ጥምቀቱም መርቆሬዎስ ተባለ ።
<h5>ለምን መከራን ተቀበለ?</h5>
1, ስለመንግስተ ሰማያት ሐዋ14÷22
2, ሃይማኖትን ለመመስከር ማቴ10÷32
3, አርአያ ለመሆን
4, እውነትን በሐሰት መለወጥ ስላልፈለገ
2ተኛ ቆሮ 5÷13


==ስለመርቆሬዎስ በአጭሩ==
==ስለመርቆሬዎስ በአጭሩ==

እትም በ19:28, 4 ዲሴምበር 2021

ቅዱስ መርቆሬዎስ

የሮም ንጉሥ የዳክዮስ ጦር ጠቅላይ አዛዥ
ሰማዕት
የተወለደበት ዘመን ፪፻፸፩ ዓም [1]
የትውልድ ቦታ ሮም
የመጀመሪያ ስሙ ፒሉፖዴር
የክርስትና ስሙ መርቆሬዎስ
የአባት ስም ሎሪዮ
የእናት ስም ክሪስቲና
ሃይማኖት ክርስትና
በዓለ ንግሥ ባረፈበት ቀን ኅዳር ፳፭ ቀን ፫፻፲ ዓም
የሚከበረው በምሥራቅም በምዕራብም ቤተክርስቲያኖች
ቤተ መርቆሬዎስን ይመልከቱ


የመጀመሪያ ስሙ ፒሉፖዴር ይባል ነበር በላቲን ሲሆን ትርጔሜውም ታማኝ ሐቀኛ ማለት ነው ። የክርስትና ስሙ መርቆሬዎስ ሙያውም ውትድርና ዜግነቱም ሮማዊ ነው ።

ይህ ታማኝ ምስክርነት የሰጠ ሰማዕት ወላጆቹ ጣዖት የሚያመልኩ አረማውያን ነበሩ።ከጊዜ ወደ ጊዜ የክርስትና እምነት እየተስፋፋ ስለ ሄደ ቤተሰቦቹም ክርስቲያኖች ሆነዋል። እሱም ካደገ በኋላ ተምሮና አምኖ ተጠመቀ ስመ ጥምቀቱም መርቆሬዎስ ተባለ ።

ለምን መከራን ተቀበለ?

1, ስለመንግስተ ሰማያት ሐዋ14÷22 2, ሃይማኖትን ለመመስከር ማቴ10÷32 3, አርአያ ለመሆን 4, እውነትን በሐሰት መለወጥ ስላልፈለገ

  2ተኛ ቆሮ 5÷13

ስለመርቆሬዎስ በአጭሩ

መርቆሬዎስም ማለት የእየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ሲሆን ይህም ቋሚ መጠርያ ስሙ ሆኖ ቀረ ። በእንግሊዞች የተጻፈው ገድለ ቅዱሳን ባዮግራፊ ኦፍ ሴንትስ እንደሚለው ዜግነቱ ኢጣሊያዊ ሲሆን ስሙንም መርኮርዮ ብሎታል የእባቱንም ስም ሎሪዮ የእናቱንም ስም ክርስቲና እንደሆነ ገልጿል ። በያመቱ ኅዳር ፳፭ ቀን የሚነበበው መጽሐፈ ስንክሳር ደግሞ የአባቱን ስም ኖኅ የናቱን ስም ታቦት የራሱንም ስም መርቆሬዮስ እንደሆነ ይገልጻል ። በዚያም ዘመን ውትድርና የተወደደና የተከበረ ሙያ ስለነበር መርቆሬዎስም ዳክዮስ ለተባለ ንጉሥ ወታደር ሆነ ዕለት ከዕለት የሚያሳየው ወታደራዊ ሥነ ሥርዓትና በሚፈጽመው ጀብዱ ከሌሎች ወታደሮች ይልቅ ተወዳጅነትና ባለሟልነት አገኘ ፤ ዳክዮስ ጠላቱን ድል አድርጎ በተመለሰ ቁጥር ድል ያስገኘለትን እግዚአብሔርን ዘንግቶ ድል የሚያስገኝለት ጣዖት እየመሰለው ከጦርነት ሲመለስ ለጣዖት መሥዋዕት የማቅረብ ልማድ ነበረው ከዕለታት አንድ ቀን ዳክዮስ መርቆርዮስን አስከትሎ ዘመተና ጠላቱን ድል አድርጎ በተመለሰ ጊዜ እንደ ልማዱ ለማይሰማውና ለማይናገረው ጣዖት ከስግደትና ከጸሎት ጋር የምስጋና መሥዋት አቀረበ ከደስታው ብዛት የተነሣ ብዙ እንሰሳት በየዓይነቱ እየመረጠ ሠዋ።

የመርቆሬዎስ ጀግንነትን የሚገልጽ ስዕል

ሰማዕት የሆነበት ምክኒያት

ቅዱስ መርቆሬዎስም ይህን በማየቱ ሰው ድል ለሰጠው ለእግዚአብሔር በመስገድና እሱንም በማመስገን ፈንታ እንዴት ሰው ለሠራው ጣዖት ይሰግዳል ? በማለት ቅር ስላለውና አረማዊነቱንም በግልጽ ስላወቀ በዚህ ተቀይሞ ወደተዘጋጀው የድል ግብዣ ሳይሄድ ቀረ በዚሁ ጊዜ አብረው የዘመቱ ሌሎች የሠራዊቱ አባሎች እኛ ለምታመልከው ጣዖት ስንሰግድና ባደረከው ታላቅ ግብዣ ትእዛዝህን አክብረን ስንገኝ ታማኝ ባለሟልህ መርቆርዎስ ትእዛዝህን በመናቅና አንተን ባለማክበር እነሆ አልተገኘም እንዲያውም ለጣዖትህ መስገድ የማይፈልግ ሳይሆን አይቀርም አስተያየት ስጥበት ብለው በንጉሡ መሾምና መወደድ የሚፈልጉ ሰዎች አሳጡት።

ዳክዮስም በመርቆሬዎስ ላይ የቀረበውን ክስ ካዳመጠ በኋላ መርቆርዎስን አስጠርቶ ስለምን ለጣዖት እንዳልሰገደና መሥዋዕት እንዳላቀረበ እንዲሁም ወደ ግብር እንዳልመጣ ጠየቀው ። እሱም ሳይፈራ በድፍረት እንኳንስ እኔ ለጣዖትህ ልሰግድና መሥዋዕት ላቀርብ አንተም እንዲህ በማድረግህ አዝናለሁ ብሎ መለሰለት ፤ ነገር ግን እኔ እግዚአብሔር አመልካለሁ ፤ ለሱም እሰግዳለሁ ይኸው መሣሪያህንና ትጥቅህን ተረከበኝ ብሎ አውልቆ ወረወረለት።ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ መስቀል መሸከሙንና ወንጌል ይዞ የክርስቶስ ወታደርነቱን በመግለጹ ዳክዮስ በጣም ተናደደ በግርፋትና በእስራት እንዲያሰቃዩትም አዘዘ ። በእስር ቤት ሲሰቃይ ሳለ የሮም ዜጋ ሆኖ በመታሰሩና በመሰቃየቱ የሮም ዜጋ መታሰሩንና መሰቃየቱን ያወቁ መገረፉንም የሰሙ እንደሆነ ሮማውያን ታላቅ ኃይል ያስከትሉብናል የሚነሣውንም ዐመፅ ለመቋቋም ስለማይቻል ግዛታችን ሰፊ ነውና በጽኑ እስራትና በግዞት እንዲሰቃይ ወደ ቂሣርያ እንላከው ሲሉ ተማከሩ ። ዳክዮስና አማካሪዎቹ በዚሁ በመስማማታቸው ታማኙ ሰማዕት ወደዚችው አገር ተላከ ቂሣርያም የምትገኘው በምድረእስራኤል ነው ።

ማርቆሬዎስ በቄሣሪያ

በቂሣርያም እስር ቤት ስቃዩንና መከራውን ተቋቋመ ወንጌል እየሰበከና እስረኞችን ከአረማዊነት ወደ ክርስትና እምነት እየለወጠ ስላስቸገራቸው ኅዳር ፳፭ ቀን ፫፻፲ ዓ/ም በሰይፍ ተከልሎ በሰማዕትነት ዐረፈ። እንደ ቅዱስ መርቆሬዎስ ስለ ታማኝ ምስክር ዮሐንስ በራእዩ በም:፫፥፲፪ እንዲህ ሲል ጽፎታል፡

"ድል የነሣውን በአምላኬ መቅደስ ዐምድ እንዲሆን አደርገዋለሁ ፤ ወደፊትም ከዚያ ከቶ አይወጣም የአምላኬን ከተማ ስም ማለት ከሰማይ ከአምላኬ ዘንድ የምትወርደውን አዲሲቱን ኢየሩሳሌም አዲሲቱን ስሜን በእርሱ ላይ እጽፋለሁ..."ብሏል።

እርግጥም ቅዱስ መርቆሬዎስ ወደ አዲሲቱ ከተማ ወደ ኢየሩሳሌም ገብቷል።

መረጃ

  1. ^ ታሪካቸው በኢትዮጵያ ሥንክሳር ወይም Ethiopian Synaxarium በኅዳር ፳፭ የሰማዕታትና ቅዱሳን ታሪክ ውስጥ ይነበባል