ከ«የንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
Requesting speedy deletion (Spam). (TwinkleGlobal)
Tag: Reverted
rv?
Tag: Manual revert
መስመር፡ 1፦ መስመር፡ 1፦
[[ስዕል:Nicaea icon.jpg|320px|thumb]]
<noinclude>{{ለማጥፋት|1=Spam}}</noinclude>
'''የንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት''' በአብዛኞቹ አብያተ ክርስቲያናት የሚቀበል የ[[ክርስትና]] እምነት መግለጫ ነው።
የንቅያው የሃይማኖት ጸሎት ወይም የእምነት መገለጫ (ጽር. Σύμβολον τῆς Νικαίας) በ፫፻፲፯ ዓ.ም. በሠለስቱ ምእት ተደንግጎ በኋላ በ፫፻፸፫ በቍስጥንጥንያ ዓ.ም. ተሻሽሏል ። የተሻሻለው መግለጫ የንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት ወይም '''የንቅያ-ቍጥንጥንያ ጸሎተ ሃይማኖት''' በመባል ይታወቃል ።


እንዲያውም የዛሬው ጸሎት ከ[[ንቅያ ጉባኤ]] በኋላ፣ በ[[ቁስጥንጥንያ ጉባኤ]] የተዘጋጀው ነው። ሁለተኛው ጉባኤ አንዳንድ ቃላት በተለይም ስለ መንፈስ ቅዱስ በይበልጥ የሚገለጽ ቋንቋ ጨመረ። በመጀመርያውም እትም፣ መጨረሻው ዓረፍተ ነገር ሀረ ጤቆች ይወገዙ ይል ነበር፤ በዚህ ፈንታ አዲሱ ጸሎተ ሃይማኖት የ[[ጥምቀት]]፣ [[የሙታን ትንሳኤ]]ና ዘላለም ሕይወት እምነቶች ይጠቅሳል።
'''<u>የመጀመርያው (የንቄያ ጉባኤው) ጸሎተ ሃይማኖት በጽርእ ፦</u>'''


ከ372 ዓም ጀምሮ እስካሁን በምንም ሳይቀየር በ[[ተዋሕዶ]]፣ [[ምሥራቅ ኦርቶዶክስ]]፣ [[ሮማን ካቶሊክ]]ና [[ፕሮቴስታንት]] አብያተ ክርስቲያን ሁሉ በሙሉ ይቀበላል። [[ሞርሞኖች]] ወይም [[የይሆዋ ምሥክሮች]] ግን [[ሥላሴ]]ን የማይቀበሉ እምነቶች ናቸው።
Πιστεύομεν εἰς ἕνα Θεὸν Πατέρα παντοκράτορα, πάντων ὁρατῶν τε καὶ ἀοράτων ποιητήν·


==የሃይማኖት ጸሎት (የተሻለው 372 ዓ.ም. ቁስጥንጥንያ እንደ ተዘጋጀ)==
καὶ εἰς ἕνα Κύριον Ἰησοῦν Χριστόν τὸν Υἱὸν τοῦ Θεοῦ, γεννηθέντα ἐκ τοῦ Πατρὸς [μονογενῆ, τοὐτέστιν ἐκ τῆς οὐσίας τοῦ Πατρός, Θεὸν ἐκ Θεοῦ,] Φῶς ἐκ Φωτός, Θεὸν ἀληθινὸν ἐκ Θεοῦ ἀληθινοῦ, γεννηθέντα, οὐ ποιηθέντα, ὁμοούσιον τῷ Πατρί,


ኹሉን በያዘ፣ ሰማይንና [[ምድር]]ን፥ የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ፡ አንድ አምላክ በሚኾን፡ በ[[እግዚአብሔር]] አብ እናምናለን።
δι' οὗ τὰ πάντα ἐγένετο, [τά τε ἐν τῷ οὐρανῷ καὶ τὰ ἐν τῇ γῇ,]


ዓለም ሳይፈጠር፡ ከእርሱ ጋራ በነበረ፥ አንድ የአብ ልጅ፥ አንድ ጌታ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር ወልድም እናምናለን። እርሱም፡ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን፥ ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ፥ የተወለደ እንጂ፡ ያልተፈጠረ፣ በመለኮቱ፡ ከአብ ጋራ የሚተካከል፣ ኹሉ፡ በእርሱ የኾነው፡ [[ኢየሱስ ክርስቶስ]] ነው። በሰማይ ካለው፣ በምድርም ካለው፡ ያለእርሱ፡ ምንም ምን፡ የኾነ የለም።
τὸν δι' ἡμᾶς τοὺς ἀνθρώπους καὶ διὰ τὴν ἡμετέραν σωτηρίαν κατελθόντα καὶ σαρκωθέντα καὶ ἐνανθρωπήσαντα,


ስለእኛ ስለሰዎች፥ እኛን ለማዳን፡ ከሰማይ ወረደ፤ በ[[መንፈስ ቅዱስ]] ግብር፡ ከቅድስት [[ድንግል ማርያም]]፡ ከሥጋዋ፡ ሥጋ፥ ከነፍሷ፡ ነፍስ ነሥቶ፡ ፍጹም ሰውን ኾነ። በ[[ጴንጤናዊው ጲላጦስ]] ዘመን፡ ስለእኛ፡ መከራን ተቀበለ። ተሰቀለ። ሞተ። ተቀበረ። በሦስተኛውም ቀን፡ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ። በክብር፥ በምስጋና፡ ወደሰማይ ዐረገ። በአባቱም ቀኝ፡ በዙፋኑ ተቀመጠ። ዳግመኛም፡ በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ፡ በምስጋና ይመለሳል። ለመንግሥቱ፡ ፍጻሜ የለውም።
παθόντα, καὶ ἀναστάντα τῇ τρίτῃ ἡμέρᾳ, ἀνελθόντα εἰς τοὺς οὐρανούς,


በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም እናምናለን። እርሱም፡ ሕይወትን የሚሰጥ፣ ከአብ የሠረፀና በነቢያት ዐድሮ የተናገረው፥ በሓዋርያት ላይ የወረደውና በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት፡ ዓለሙን፡ በጸጋው የሞላው፡ ቅዱሱ የእውነት መንፈስ ነው። ለእርሱም፡ ከአብና ከወልድ ጋራ፡ በአንድነት እንሰግድለታለን፤ እናመሰግነዋለንም።
ἐρχόμενον κρῖναι ζῶντας καὶ νεκρούς.


በአንዲት ቅድስት ካቶሊክ እና ሐዋርያዊት<ref>በኢ.ኦ.ተ.ቤ አገልግሎት በተጨማሪ እንዲህ ይላል፦ «ኢየሱስ ክርስቶስ፡ ጥንት፡ በቀደሙት ሰዎች ኪዳነ ልቦና በመሠረታት፥ በነቢያት ቃል ባጸናትና በሓዋርያት ጕባኤ በፈጸማት፥ ካህናት፡ የእርሱን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም፡ ለመሥዋዕትነት በሚያቀርቡባት፥ ምእመናንና ምእመናትም፡ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋዎች በሚቀበሉባት፡ በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን።» [http://www.medhanialemeotcks.org/about/our-belief/ ጸሎተ ሃይማኖት በግዕዝና በአማርኛ]</ref> ቤተ ክርስቲያን እናምናለን።
Καὶ εἰς τὸ Ἅγιον Πνεῦμα.


ኃጢኣት በሚሠረይባት፡ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን።
[Τοὺς δὲ λέγοντας, Ἦν ποτε ὅτε οὐκ ἦν, καὶ Πρὶν γεννηθῆναι οὐκ ἦν, καὶ ὅτι Ἐξ οὐκ ὄντων εγένετο, ἢ Ἐξ ἑτέρας ὑποστάσεως ἢ οὐσίας φάσκοντας εἶναι, ἢ κτιστόν, ἢ τρεπτόν, ἢ ἀλλοιωτὸν τὸν Υἱὸν τοῦ Θεοῦ, τούτους ἀναθεματίζει ἡ ἁγία καθολικὴ καὶ ἀποστολικὴ ἐκκλησία].


በሙታን ትንሣኤ፥ በዘለዓለምም ሕይወት እናምናለን። ለዘለዓለሙ፤ አሜን።
'''<u>የተሻሻለውና አኹን ጥቅም ላይ ያለው (የንቅያ-ቍስጥንጥንያው) ጸሎተ ሃይማኖት በጽርእ ፦</u>'''


==በመጀመርያው ንቅያ ጉባኤ በ317 ዓ.ም. እንደ ተጻፈ==
Πιστεύομεν εἰς ἕνα Θεὸν Πατέρα παντοκράτορα, ποιητὴν '''οὐρανοῦ καὶ γῆς,''' ὁρατῶν τε πάντων καὶ ἀοράτων.


ኹሉን በያዘ፣ የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ፡ አንድ አምላክ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን።
Καὶ εἰς ἕνα Κύριον Ἰησοῦν Χριστόν, τὸν Υἱὸν τοῦ Θεοῦ '''τὸν μονογενῆ''', τὸν ἐκ τοῦ Πατρὸς γεννηθέντα '''πρὸ πάντων τῶν αἰώνων''', φῶς ἐκ φωτός, Θεὸν ἀληθινὸν ἐκ Θεοῦ ἀληθινοῦ, γεννηθέντα οὐ ποιηθέντα, ὁμοούσιον τῷ Πατρί·


ከእርሱ ጋራ በነበረ፥ የአብ ልጅ፥ አንድ ጌታ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር ወልድም እናምናለን። እርሱም፡ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን፥ ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ፥ የተወለደ እንጂ፡ ያልተፈጠረ፣ በመለኮቱ፡ ከአብ ጋራ የሚተካከል፣ ኹሉ፡ በእርሱ የኾነው፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በሰማይ ካለው፣ በምድርም ካለው፡ ያለእርሱ፡ ምንም ምን፡ የኾነ የለም።
δι' οὗ τὰ πάντα ἐγένετο·


ስለእኛ ስለሰዎች፥ እኛን ለማዳን፡ ወረደ፤ ነፍስ ነሥቶ፡ ፍጹም ሰውን ኾነ። መከራን ተቀበለ። በሦስተኛውም ቀን፡ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ። ወደሰማይ ዐረገ። ዳግመኛም፡ በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ፡ ይመለሳል።
τὸν δι' ἡμᾶς τοὺς ἀνθρώπους καὶ διὰ τὴν ἡμετέραν σωτηρίαν κατελθόντα '''ἐκ τῶν οὐρανῶν''' καὶ σαρκωθέντα '''ἐκ Πνεύματος Ἁγίου καὶ Μαρίας τῆς παρθένου''' καὶ ἐνανθρωπήσαντα,


በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም እናምናለን።
'''σταυρωθέντα τε ὑπὲρ ἡμῶν ἐπὶ Ποντίου Πιλάτου, καὶ''' παθόντα '''καὶ ταφέντα''', καὶ ἀναστάντα τῇ τρίτῃ ἡμέρᾳ '''κατὰ τὰς γραφάς''', καὶ ἀνελθόντα εἰς τοὺς οὐρανούς, '''καὶ καθεζόμενον ἐκ δεξιῶν τοῦ Πατρός''',


ነገር ግን፣ «ያልተገኘበት ዘመን ነበር» እና «ሳይፈጠር አልነበረም» እና «ከአንዳችም ተፈጠረ»፣ ወይም «ከሌላ ባሕርይ ነው» ወይም «የእግዚአብሔር ወልድ ይፈጠራል» ወይም «የሚለወጥ ነው» የሚሉት፦ በቅድሥት ካቶሊክ እና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን ዘንድ ይወገዙ።
καὶ '''πάλιν''' ἐρχόμενον '''μετὰ δόξης''' κρῖναι ζῶντας καὶ νεκρούς·


==ዋቢ ምንጭ==
οὗ τῆς βασιλείας οὐκ ἔσται τέλος.
<references/>


Καὶ εἰς τὸ Πνεῦμα τὸ Ἅγιον, '''τὸ Κύριον, τὸ ζῳοποιόν, τὸ ἐκ τοῦ Πατρὸς ἐκπορευόμενον, τὸ σὺν Πατρὶ καὶ Υἱῷ συμπροσκυνούμενον καὶ συνδοξαζόμενον, τὸ λαλῆσαν διὰ τῶν προφητῶν. Εἰς μίαν, ἁγίαν, καθολικὴν καὶ ἀποστολικὴν Ἐκκλησίαν· ὁμολογοῦμεν ἓν βάπτισμα εἰς ἄφεσιν ἁμαρτιῶν· προσδοκοῦμεν ἀνάστασιν νεκρῶν, καὶ ζωὴν τοῦ μέλλοντος αἰῶνος. Ἀμήν'''.

'''<u>የንቅያው ጸሎተ ሃይማኖት አንድምታና ዐማርኛ ንባቡ ፦</u>'''

፩- ሁሉን በያዘ ሰማይንና ምድርን የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ በአንድ አምላክ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን። ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች አንድ አምላክ ስለሆነ እግዚአብሔርና ስለ ፍጥረቱ ይናገራሉ፦  እግዚአብሔር በስድስት ቀን ሰማይንና ምድርን፥ ባሕርንም፥ ያለባቸውንም ሁሉ ፈጥሮ በሰባተኛው ቀን ዐርፎአልና።ዘጸ.፳፡፲፩  አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው፤ ዘዳ.፮፡፬  ዓይናችሁን ወደ ላይ አንሥታችሁ ተመልከቱ፤ እነዚህን የፈጠረ ማን ነው? ሠራዊታቸውን በቍጥር የሚያወጣ እርሱ ነው... በኃይሉ ብዛትና በችሎቱ ብርታት አንድስ እንኳ አይታጣውም። ኢሳ.፵፤፳፮  እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ ከእኔ ሌላም የሚያድን የለም። ኢሳ.፵፬፡፲፩  እኔ እግዚአብሔር ነኝ ከእኔም ሌላ ማንም የለም፤ ከእኔም በቀር አምላክ የለም፤ በፀሐይ መውጫና በምዕራብ ያሉ ከእኔ በቀር ማንም ሌላ እንደሌለ ያውቁ ዘንድ አስታጠቅሁህ፥ አንተ ግን አላወቅኸኝም፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ ከእኔም ሌላ ማንም የለም። እሳ.፵፭፡፭-፮  እኔ እግዚአብሔር ነኝ ከእኔም ሌላ ማንም የለም፤ ከእኔም በቀር አምላክ የለም፤ በፀሐይ መውጫና በምዕራብ ያሉ ከእኔ በቀር ሌላ እንደሌለ ያውቁ ዘንድ አስታጠቅሁህ ግን አላወቅኸኝም፤ ኢሳ.፵፭፡፲፰  ለእኛስ ነገር ሁሉ ከእርሱ የሆነ እኛም ለእርሱ የሆንን አንድ አምላክ አብ አለን፥ ፩ ቆሮ.፰፡፮  ከሁሉ በላይ የሚሆን በሁሉም የሚሠራ በሁሉም የሚኖር አንድ አምላክ የሁሉም አባት አለ። ኤፌ.፬፡፮

፪- ዓለም ሳይፈጠር ከእርሱ ጋር በነበረ የአብ አንድ ልጅ በሚሆን በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን። ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ስለ አብ አንድ ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ማመንን ይናገራሉ፦  በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። ዮሐ.፫፡፲፮  በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን አንተና ቤተ ሰዎችህ ትድናላችሁ አሉት። ሐዋ.፲፮፡፴፩  እኛም በእርሱ በኩል የሆንን አንድ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አለን። ፩ ቆሮ.፰፡፮  ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው። ፊል.፪፡፲-፲፩  አንተ ልጄ ነህ፥ እኔ ዛሬ ወልጄሃለሁ፥ ደግሞም። እኔ አባት እሆነዋለሁ እርሱም ልጅ ይሆነኛል። ዕብ.፩፡፭  ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ... ይህ ተጽፎአል። ዮሐ.፳፡፴፩  አባት ሆይ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ። ዮሐ.፲፯፤፭

፫- ከብርሃን የተገኘ ብርሃን፤ ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ፤ የተፈጠረ ያይደለ የተወለደ፤ በመለኮቱ ከአብ ጋር የሚተካከል። ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ከብዙ በጥቂቱ የአብና የወልድን እኩል መሆን ይናገራሉ፦  በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። ዮሐ.፩፡፩  እኔና አብ አንድ ነን። ዮሐ.፲፡፴፤  እኔን ያየ አብን አይቶአል። ዮሐ.፲፬፡፱  ለአብ ያለው ሁሉ የእኔ ነው። ዮሐ.፲፮፡፲፭  ከአብ ወጥቼ ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ ደግሞ ዓለምን እተወዋለሁ ወደ አብም እሄዳለሁ። ዮሐ.፲፮፡፳፰  ብርሃንም ወደ ዓለም ስለ መጣ ሰዎችም ሥራቸው ክፉ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለ ወደዱ ፍርዱ ይህ ነው። ዮሐ.፫፡፲፱

፬-ሁሉ በእርሱ ሆነ ያለ እርሱ ምንም ምን የሆነ የለም፤ በሰማይም ያለ በምድርም ያለ። ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ከብዙ በጥቂቱ ሁሉም ነገር በወልድ እንደሆነ ይናገራሉ፦  ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም። ዮሐ.፩፡፫  እርሱም የማይታይ አምላክ ምሳሌ ነው። የሚታዩትና የማይታዩትም፥ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት፥ በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋልና ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኵር ነው። ሁሉ በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል። ቆላ.፩፡፲፮

፭- ስለ እኛ ስለ ሰዎች ስለመዳናችን ከሰማይ ወረደ። በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፈጽሞ ሰው ሆነ። ከዚህ በታች ያሉት ጥቅሶች ከሰማይ መውረዱንና ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን ይናገራሉ፦  እነሆ ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።ኢሳ.፯፡፲፬  እናቱ ማርያም ለዮሴፍ በታጨች ጊዜ ሳይገናኙ ከመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች። ማቴ.፩፡፲፰  የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤ ገላ.፬፡፬

፮- ሰው ሆኖ በጰንጤናዊው በጲላጦስ ዘመን ስለእኛ ተሰቀለ፤ ታመመ፤ ሞተ፤ ተቀበረ፤ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፤ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈ። ከዚህ በታች ያሉት የተዘረዘሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የወልድን ሕማሙን፣ ሞቱንና ትንሣኤውን ይናገራሉ፦  ጲላጦስም ሁከት እንዲጀመር እንጂ አንዳች እንዳይረባ ባየ ጊዜ፥ ውኃ አንሥቶ። እኔ ከዚህ ጻድቅ ሰው ደም ንጹሕ ነኝ፤ እናንተ ተጠንቀቁ ሲል በሕዝቡ ፊት እጁን ታጠበ። ማቴ.፳፯፡፳፬  በዚያን ጊዜ በርባንን ፈታላቸው፥ ኢየሱስን ግን ገርፎ ሊሰቀል አሳልፎ ሰጠ። ማቴ.፳፯፡፳፮  ኢየሱስም ሁለተኛ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ተወ።  ጲላጦስም እንዲሰጡት አዘዘ። ዮሴፍም ሥጋውን ይዞ በንጹሕ በፍታ ከፈነው፥ ከዓለት በወቀረው በአዲሱ መቃብርም አኖረው፥ በመቃብሩም ደጃፍ ታላቅ ድንጋይ አንከባሎ ሄደ። ማቴ.፳፯፡፶፱  እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ። ማቴ.፳፰፡፮  ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም። ሉቃ.፳፬፡፭  አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል። ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና። ፩ቆሮ.፲፭፡፳-፳፩

፯- በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ፤ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ። ዳግመኛም ሕያዋንንና ሙታንን ይገዛ ዘንድ በጌትነት ይመጣል። ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም። ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የወልድን ዕርገቱን እና ዳግም መምጣቱን ይናገራሉ፦  ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ። ሉቃ.፳፬፡፶፩  በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፥ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም። ሉቃ.፩፡፴፫  ከሰማይ ከወረደ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው። ዮሐ.፫፡፲፫  ይህንም ከተናገረ በኋላ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው። ሐዋ.፩፡፱  ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ። ሐዋ.፯፡፶፮  የሰው ልጅ ከመላእክቱ ጋር በአባቱ ክብር ይመጣል፤ለሁሉ እንደ ሥራው ያስረክበዋል። ማቴ.፲፮፡፳፯  ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ። ፩ተሰ. ፬፡፲፮

፰- ጌታ ማኅየዊ በሚሆን ከአብ በሰረፀ በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን፤ እንሰግድለት እናመሰግነውም ዘንድ ከአብና ከወልድ ጋር በነቢያት የተናገረ። ከዚህ በታች ያሉት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ስለ መንፈስ ቅዱስና ለመንፈስ ቅዱስ የሚገባውን ክብር ይናገራሉ፦  እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ከእናንተ ጋር ነኝ። ማቴ.፳፰፡፲፱-፳  እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ አጽናኝ እርሱም ከአብ የሚወጣ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ፥ እርሱ ስለ እኔ ይመሰክራል። ዮሐ.፲፭፡፳፮  ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ። ፪ጴጥ.፩፡፳፩  መንፈስም እውነት ነውና የሚመሰክረው መንፈስ ነው። የሚመሰክሩት መንፈሱና ውኃው ደሙም ሦስት ናቸውና፤ ሦስቱም በአንድ ይስማማሉ። ፩ዮሐ.፭፡፰

፱- ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰብዋት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን። ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይናገራሉ፦  አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም። ማቴ.፲፮፡፲፰  ባሎች ሆይ፥ ክርስቶስ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት ሚስቶቻችሁን ውደዱ። ኤፌ.፭፡፳፭  ...እነርሱንም ባይሰማ፥ ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፤ ደግሞም ቤተ ክርስቲያንን ባይሰማት፥ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ። ማቴ.፲፰፡፲፯

፲- ኃጢአትን ለማስተሥረይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን። ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ስለ ጥምቀት ይናገራሉ፦  ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል። ማር.፲፮፡፲፮  ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው። ዮሐ.፫፡፭  ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ። ሐዋ.፪፡፴፰  አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት፤ ኤፌ.፬፡፭

፲፩- የሙታንንም መነሣት ተስፋ እናደርጋለን። ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ስለ ትንሣኤ ሙታን ይናገራሉ፦  በምድርም ትቢያ ውስጥ ካንቀላፉቱ ብዙዎች ይነቃሉ፤ እኵሌቶቹ ወደ ዘላለም ሕይወት፥ እኵሌቶቹም ወደ እፍረትና ወደ ዘላለም ጕስቍልና። ዳን.፲፪፡፪  በመቃብር ያሉቱ ሁሉ ድምፁን የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል፤ መልካምም ያደረጉ ለሕይወት ትንሣኤ ክፉም ያደረጉ ለፍርድ ትንሣኤ ይወጣሉና። ዮሐ.፭፡፳፱

፲፪- የሚመጣውንም ሕይወት ለዘለዓለሙ አሜን። ከዚህ በታች ያለው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ስለ ዘላለማዊ ሕይወት ይናገራል፦  እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት። ዮሐ.፲፯፡፫

'''<u>ሐተታ፦</u>'''

ቤተ ክርስቲያን ሰማያዊት ንጽሕትና ቅድስት የክርስቶስ ማደሪያ ናት። መጽሐፍ ቅዱስ «በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቋት ዘንድ እናንተን ጰጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለራሳችሁ እና ለመንጋው ሁሉ ተጠንቀቁ» በማለት ያስጠነቅቃል። በሰው ልጅ ፈቃድና ሐሳብ ያልተሠራች እግዚአብሔር በደሙ የዋጃት ቅድስት ሥፍራ ናት። ቤተ ክርስቲያን በሰማይና በምድር ያለች፣ ከሰው ልጅ ዕውቀት ፈቃድና ፍላጎት በላይ የሆነች የእግዚአብሔር ማደሪያ ናት። እግዚአብሔር የመሠረታት፣ የቀደሳትና የዋጃት፣ ሐዋርያት፣ ነቢያትና ቅዱሳን አበው የሰበኳትና ያጸኗት ቤት ናት፤ ለሰውም በረከተ ሥጋንና በረከተ ነፍስን ታድላለች።

ይህን ሁሉ እያደረገች በጉዞዋ ቤተ ክርስቲያን ከፈተና ወጥታ አታውቅም። በፈተና ውስጥ ያለፈች የኖረችና ለወደፊቱም የምትኖር ቤት ናት። የቤተ ክርስቲያን ፈተና የተጀመረው በሰማይ በዓለመ መላእክት ነው። የቀደመው የመላእክት አለቃ የነበረው ሳጥናኤል አምላክነትን ሽቶ ከቅዱሳን መላእክት ጋር በመዋጋት ተሸንፏል፣ ወድቋል፣ ተዋርዷል ቅድስናውን አጥቶ ረክሷል፤ ከሰማይ ከክብሩ እና ከሥልጣኑም ተባሯል። ዛሬ ብዙዎች ቤተ ክርስቲያንን የሚዋጉት ለቅድስና ብለው አይደለም። ዛሬም ምድራዊ ክብርን፣ ዝናንና ሥልጣንን ፈልገው ሆዳቸው አምላካቸው የሆኑ መናፍቃንና ጀሌዎቻቸው ቤተ ክርስቲያንን ይፈታተኗታል። እነርሱ ይጠፋሉ እንጂ ቤተ ክርስቲያን ግን ለዘለዓለሙ ትኖራለች።

በተለያዩ ዘመናት በቤተ ክርስቲያን ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች ቅዱሳን አባቶች መንፈስ ቅዱስን ኃይል አጋዥ በማድረግ መልስ ሲሰጡ ነበር፤ አሁንም ይሰጣሉ። ክርስትና እውነት ነው፣ ከሥልጣን ከክብር ከዝና ከታላቅነትና ከታዋቂነት በላይ ነው። አባቶች በየዘመናቱ ቤተ ክርስቲያን ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች መልስ ሰጥተዋል። በተለያዩ ዘመናት ለተነሡት የቤተ ክርስቲያን ጥያቄዎች መልሶች ተሰጥተዋል። ከእነዚህ መልሶች ውስጥ የኒቅያ ጉባኤ (፫፻፳፭) የቁስጥንጥንያ ጉባኤ (፫፻፹፩) እና የኤፌሶን ጉባኤ (፬፻፵፩) ጉባኤያት ቀደምትና ዋና ዋና መልሶች የተሰጡባቸው ጉባኤያት ናቸው። የኒቅያ ጉባኤ በአርዮስ የክሕደት የሐሰት፤ የጥፋትና የምንፍቅና ትምህርትን መሠረት በማድረግ በኒቅያ ከተማ ፫፻፲፰ ቅዱሳን አባቶች የተሰበሰቡበት የቁስጥንጥንያ ጉባኤ ደግሞ የመቅዶንዮስን የስሕተት ትምህርትን መሠረት በማድረግ ፻፶ ሊቃውንት በ፫፻፹፩ ዓ.ም. በቁስጥንጥንያ የተሰበሰቡበት የኤፌሶን ጉባኤ ደግሞ የንስጥሮስን ትምህርት ለማውገዝ በ፬፴፩ ዓ.ም ፪፻ አበው በኤፌሶን ከተማ በመሰብሰብ መናፍቃንን በመለየት እምነትን አጽንተዋል።

በአሁኑ ጊዜ በኦሮሚያ ክልል የራሱ ቤተ ክህነት ይቋቋምለት በሚል ጉባኤ በማዘጋጀት ከቅዱስ ሲኖዶሱ ዕውቅና ውጪ የሆነ ሐሳብ ማቅረቡ በሚዲያ እየተዘገበ ነው። የተነሱት ቅራኔዎች በመላው የኦሮሚያ ክልል የቤተ ክርስቲያን አገልግሎትን ተደራሽ አላደረገም የሚል ሲሆን ይህን ጥያቄ መነሻ በማድረግ ቅዳሴ፤ ስብከት እንዲሁም ሌሎች መጽሐፎች በኦሮምኛ ቋንቋ መተርጎማቸውንና ለክልሉ ሰዎች ተደራሽም ማድረግ እንደተቻለ በውይይቱ ተገልጿል። ይህ ሁለተኛው ጥያቄ ክልሉ የራሱ ቤተ ክህነት ይቋቋምለት የሚለው ግን አሁን የተነሳ ሐሳብ ከመሆኑም ባሻገር ከሃይማኖት አባቶች በተማርነው መሠረት ቤተ ክርስቲያን ስለማትገነጠል ቋንቋም ስለማይገድባት ይህን ሐሳብ በመንቀፍ ተቃውሞ ቀርቦባቸዋል፤ አካሄዳቸውንም ማስተካከል እንዳለባቸውና ቅዱስ ሲኖዶስ እንደማይቀበለው አሳስበዋል።

«በቅዱስ ሲኖዶሱ ተወስኖ፤ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ ታምኖበት በውይይት ሐሳብ ይቀርብበታል እንጂ በዘፈቀደ እንዲህ ያለ ጥያቄ አቅርቦ ጉባኤ ማካሄድ አግባብ አይደለም፡፤ ጉዳቱም የሰፋ ይሆናል። ስለዚህ ነሐሴ ፳፬፤፳፻፲፩ ዓ.ም. ቀሲስ በላይ መኮንን የኦሮሚያ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት በክልል ደረጃ ለማቋቋም ያነሱትን ጥያቄ በቅዱስ ሲኖዶሱ ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ የሚመለከተው የመንግሥት አካል ድርጊቱን እንዲያስቆምልን አጥብቀን እንጠይቃለን» ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ርእሰ ደብር መሓሪ ኃይሉ  ናቸው።

«ቋሚ ሲኖዶስ ይህንን ጉዳይ የተቃወመው፤ ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጪ ስለሆነ  ነው። ሌሎች ሳይገባቸው በዚህ ዓይነት መንገድ የሚሄዱ አካሄዳቸውን እንዲያስተካክሉም ውሳኔ አስተላልፏል። ቅዱስ ሲኖዶስ ያልተቀበለውና ከቀኖና ውጪ የሆነውን ይህን ሐሳብ በመንቀፍ በደብዳቤ ለመንግሥት እንዳይተላለፍም ተደርጓል፤ መንግሥትም ማስቆም አለበት። ምክንያቱም ወደ ብጥብጥና ግጭት ስለሚያመራና የራሱን ኃላፊነት ወስዶ ማስቆም እንዳለበት ቋሚ ሲኖዶስ አስገንዝቧል» ሲሉም ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ፤የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊና የምስራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ገልጸዋል።

ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ «ከኛ ወገን ስላልሆኑ ከኛ ወጡ ዳሩ ግን ከኛ ወገን ቢሆኑ ኖሮ ከእኛ ጋር ጸንተው በኖሩ ነበር» (፩ዮሐ.፪፥፲፱) በማለት አንድነታቸውም ከክርስቲያን ወገን እና ከቅዱሳን አንድነት ያለመሆኑን ይናገራል። ቅዱሳን አባቶች በየጉባኤያቱ ላይ ለተነሱት የሐሰት ትምህርቶች መልስን ሰጥተዋል። የሥላሴን አንድነትና ሦስትነት የጌታችንን ፍጹም ሰውና ፍጹም አምላክ መሆን የመንፈስ ቅዱስን አምላክነት የእመቤታችንን ወላዲተ አምላክነትም መስክረዋል አስተምረዋል። ሃይማኖትንም አጽንተዋል። ልዩ ልዩ ሥርዓትንም ደንግገዋል። የቤተ ክርስቲያን አንድነት የሁሉም መሆኗን ቅድስትና ንጽሕት የሆነች ስለመሆኗም በቁስጥንጥንያ ጉባኤ ላይ የጽሑፋችን መነሻ ርእስ ያደርግነውን ኃይለ ቃል «ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን» በማለት  ደገኛ አባቶች ውሳኔያቸውን አጽንተዋል። ይህን ስንል ስለ ቅድስናዋ ምስክርነት ሰጡ ማለት እንጂ አስቀድማ ቅድስት አልነበረችም ማለታችን አይደለም።

መጋቤ ሰላም ሰለሞን ቶልቻ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ኃላፊ ይህን አስመልክቶ «ቤተ ክርስቲያን ዘርን፤ ነገድን፤ ጎሳን ማእከል አድርጋ አትሠራም። የሰው ልጅ ሰው በመሆኑም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ መሆኑን ከዚያም አልፎ በሰብአዊነት ላይም የምትሠራው ሕገ እግዚአብሔርን ማስተማር ነው እንጂ ሰውን በቋንቋና በጎሳ አትለይም። እንዲህ ሲባል ግን አማኞች በራሳቸው ቋንቋ ትምህርተ ወንጌል እንዲማሩ፤ የቤተክርስቲያንን ሥርዓት እንዲያውቁ ቤተክርስቲያን ሰፊ ሥርዓት ሠርታለች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መሬት ወራሪ አይደለችም። አሁን እየተነገረ ያለው መሬት ወራሪ ናት እየተባለ ምእመናንን ወደ አልተፈለገ ቦታ/  መንገድ/ ለመክተት ነው። የኦሮሚያ ክልል ተወሮ ቤተክርስቲያን አልተሠራም።  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አትከፈልም። ቋንቋ መግባቢያ እንጂ መከፋፈያ አይደለም» ብለዋል።

ከዚህ ላይ እኛም በወንጌል የተማርነውን ትምህርት ማስታወስ ግድ ይለናልና ሦስቱን የቤተ ክርስቲያን ምሥጢራዊ ትርጓሜዎች እንመልከት። ቤተ ክርስቲያን የሚለው ስም ሦስት ምሥጢራዊ ትርጓሜዎችን የያዘ ነው። እነዚህም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን፣ የምእመናን ኅብረትና የእያንዳንዱ ክርስቲያን አካል ናቸው፤ ቀጥለን እነዚህን በተናጠል እንመልከታቸዋለን።

'''፩.የክርስቲያን ሰውነት'''

እያንዳንዱ ክርስቲያን ልዩ እና ድንቅ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ነው። ይህንንም ቅዱስ ጳውሎስ ሲያስረዳ እንዲህ ጽፎልናል፤ «የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን? ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና ያውም እናንተ ናችሁ» (፩ቆሮ. ፫፥፲፮-፲፯)

የእኛ በኃጢአት መቆሸሽ ስለ ቤተ ክርስቲያን አንድነትና ለክርስቲያኖች ኅብረት እንቅፋት ነውና። «ራስን ከኃጢአት መጠበቅና በንስሓ ሕይወት መኖር ይገባናል። ክርስቶስ ዋጋ ሊተመንለት በማይችል በደሙ ገዝቶናል፤ በዋጋ ተገዝታችኋል የተባልነውም ለዚህ ነው። በሌላም በኩል ለቅዱስ ጴጥሮስ ግልገሎቼን አሰማራ ጠበቶቼን ጠብቅ በጎቼን አሰማራ ተብሎ ጥብቅ አደራ የተሠጠው ይህንን ያመለክታል (ዮሐ.፪፥፲፭-፲፯)።

'''፪. የክርስቲያኖች አንድነት፡-''' በሌላም በኩል የክርስቲያኖች አንድነት ቤተ ክርስቲያን ተብሎ ይጠራል። ይህ መንፈሳዊ ስብስብ ነው። ለመልካም ነገር ለአንድነት ለቅድስና ተብሎ የሚደረግ ስብስብ ነው። ስለ ቤተ ክርስቲያን አንድነት ስለ ቃለ እግዚአብሔር መስፋፋት ስለ ቤተ ክርስትያን አስተዳደራዊ መዋቅር መጠናከር ስለነፍሳት ድኅነት ተብሎ የሚደረግ ስብስብ ነው።

'''፫. ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን፡-''' ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን እግዚአብሔር በፈቀደ  በጭቃ በጨፈቃ፣ በዓለት በገጠር በከተማ፣ በተራራ በዋሻ፣ በዱር በገደል ልትታነጽ ትችላለች። በተለያዩ ቅዱሳን ስም ልትሰየምም ትችላለች፤ ዓላማዋ ግን አንድ ነው፤ እርሱም ሰዎች የእግዚአብሔርን ልጅነት የሚያገኙበት፣ ጸሎት የሚያደርሱበት ምስጋና የሚያቀርቡበት ሥጋ ወደሙን  የሚቀበሉበት፤ በሕይወታቸው ፍጻሜም እስከ ዳግም ምጽአት ድረስ ሥጋቸው የሚያርፍበት ቅዱስ ቤት ነው። ይህ ቤት የምስጋና፤ የጸሎት የመሥዋዕት ቤት ነው። ለዚህ ነው ጌታችን «ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል» በማለት የተናገረው። ቤተ ክርስቲያን በሥጋውያን ሰዎች ብትገለገልም የሚጠብቋት ቅዱሳን መላዕክት ናቸው። የመረጣት፤ የሚቀድሳትና የሚያከብራት ግን እግዚአብሔር ነው። በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አገልጋዮች ሊያጠፉ ይችላሉ፤ የሥነ ምግባር ጉድለትን ሊያሳዩ ይችላሉ። ይህ ግን የእነርሱ ችግር ነው እንጂ ቤተ ክርስቲያንን የሚገልጽ ጉዳይ አይደለም።

ቤተ ክርስቲያን የማንንም ወገን  (ብሔር፤ ቡድን፤ ጎሳ፤ ዘርን፤ አካባቢን፤ ክልልን) አትወክልም። ቤተ ክርስቲያን የሁሉም ናትና። ቤተ ክርስቲያን አንዲት፤ ቅድስት፤ ንጽሕት እና ሐዋርያዊት ናት። ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ አካሉ ናት ካልን የቤተ ክርስቲያንን አንድነትን ሊከፋፍሉ/ሊሸረሽሩ/ ከሚችሉ ኢ-ሥነ ምግባራዊ ተግባራትም ከመፈጸም ልንቆጠብ ይገባል። የግል ሐሳብንና ፍላጎትን የቡድን ዓላማን ለማሳካት ከተለያዩ ከቤተ ክርስቲያን መዋቅር ላይ ካሉ ግለሰቦች ጋር ያለንን ቂምና ጥላቻን እንደማሳያ ለማድረግ ብለን ቤተ ክርስቲያንን ከመክፈል ልንጠበቅ ይገባል።

ቤቱን የመረጠው እርሱ ራሱ መሆኑን ሲናገር «ለዘለዓለም ስሜ በዚያ ያድር ዘንድ ይህን የሠራኸውን ቤት ቀድሸዋለሁ መርጨዋለሁ» በማለት ገልጾታል (፩<sup>ኛ</sup>ነገ. ፱፥፫)።  ቅዱስ ዳዊት የእግዚአብሔርን ቤት ለመሥራት ፍላጎት ቢኖረውም የእግዚአብሔር ፈቃድ ግን አልነበረም። እግዚአብሔርን ማገልገል ቤቱን መጠበቅ መሥራት የራሳችን ምኞት  ቢኖርም  የእግዚአብሔር ፈቃድ ግን ያስፈልጋል። ገንዘብ ስላለን ጊዜው ስለፈቀደልን ብቻ ቤቱን መሥራት አይቻልም።

ጊዜ ጉልበት ገንዘብ ሀብት ንብረት ጥበብ ዕውቀት የእግዚአብሔር ነውና በተሰጠን ነገር መልካም ነገርን መሥራት ጥሩ ነው። ቤቱን ማስጨነቅ እግዚአብሔርን ማሳዘን ነውና። ለዚህ ነው (የሐዋ. ሥራ ፱፥፬ ላይ) «ሳውል ሳውል ለምን ታሳድደኛለህ» የተባለው። ስለቤቱ አንድነት ልዕልና ቅድስና ስናስብ ሰዎችና እግዚአብሔርም ይደሰታሉ።ከዚህ ውጪ ቤተ ክርስቲያን ላይ ክፉ ነገርን ለማድረግ ማሰብ የቤተ  ክርስቲያንን ንብረት፣ ቦታ መውሰድ፣ መንጠቅ ስናስብ እግዚአብሔርም ያዝንብናል ልንመለስ ይገባል። ጥፋቱም ከእኛ አልፎ ለትውልድ ሁሉም ይደርሳልና ወደ ልቦናችን እንመለስ። አንድነት የፍቅርና የቅድስና ብሎም የክርስትና መገለጫና መሠረት ነው። ልዩነት ግን የአሕዛባዊነት ምልክት ነው።

ጳውሎስ የተባለው ሳውል ወደ ክርስትና ሕይወት ከመጠራቱ በፊት የቤተ ክርስቲያን አንድነትን ለማጥፋት ከሚፋጠኑ አሕዛብ ወገን ነበር። ቤተ ክርስቲያንን ማሳደድ፣  ክርስቶስን ማሳደድ ነው። አንድነትን፣ ፍቅርን፣ ክርስትናን መጥላት፣ ማሳደድ፣ መከፋፈል የአሕዛባዊነት ምልክት ነውና። እግዚአብሔር ተገልጦለት «ለምን ታሳድደኛለህ» ብሎ ተናገረው፤ ሳውል ክርስቲያኖችን ለማስገደል፣ ለማሳደድና ለማሳሰር የቤተ ክርስቲያን አንድነትን ኅብረትን ለማፈራረስ ከባለሥልጣናት ደብዳቤን ያጽፍ ነበር። እግዚአብሔር የፍቅር የቸርነትና የምሕረት አምላክ ነውና በፍቅር ጠራው ንስሓም ገባ።

ቤተ ክርስቲያንን ያሳድድ የነበረው ሰው ክርስቲያን ሆነ ስለ እውነት ስለ ፍቅር ስለ አንድነት ተሰደደ፤ከመሰደድም አልፎ ተሰቀለ። ዛሬም እርሱ ይፈጽም የነበረውን ተግባርን የምትፈጽሙ ግለሰቦች ወደ ልቡናችሁ ልትመለሱ ይገባል። ጊዜውንና ሁኔታውን ተገን አድርጋችሁ ክፋትን መሥራት ቤተ ክርስቲያንን ማሳደድ የለባችሁም። የአንዳንድ ግለሰቦች ታሪክን በተለይም ከዚህ በፊት የነበሩ የአንዳንድ ነገሥታትን (መንፈሳዊና ሀገራዊ መሪዎችን ጭምር) ስሕተታቸውን ብቻ በመፈለግ ከቤተ ክርስቲያን ጋርም በማገናኘት ቤተ ክርስቲያንን የጥፋቱ ሰለባ አታድርጉአት። ይህ ደግሞ ፍጹም ስሕተተ ነው። የግለሰቦችን ታሪክ ከቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጋርም ማያያዝ የለብንም ።

መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ኃይለጊዮርጊስ ተረፈ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ መንፈሳዊ ፍርድ ቤት አባል ዳኛ እንዲህ ብለዋል፤ «ቤተክርስቲያን አንድነትን እያስተማረች፤ሰላምን እየሰበከች፤ ሁሉን ልጆቼ ብላ ይዛ አያሌ ዘመናትን አሳልፋለች ። ሀገር ወራሪ፤ አጥፊ ሲመጣም ቤተ ክርስቲያን ከልጆቿ ጋርና ከሚመለከተው አካል ጋር ሆና ዛሬ እኛ የምንኖርባትን ሀገር፤ በጸሎት በሕይወት መሥዋዕትም በመክፈል ያስጠበቀች ቤተ ክርስቲያን ናት ። ነገር ግን አሁን እየሰማን ያለነው ሂደት ፈጽሞ በቤተክርስቲያን ሕግና ሥርዓት ተቀባይነት የሌለው ነው ። ቤተ ክርስቲያን አንዲትና የሁሉም እናት ናት ።»

አንዲትና ቅድስት የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን መከፋፈል ለምን አስፈለገ? አንድነትን አፍርሶ ስለአንድነት ስለፍቅር ስለሰላም ስለቅድስና ማውራት አይቻልምና። አንድነትን አፍርሶ ማን በሰላም ያድራል? እርሱ አንድነትን ፍቅር እና ሰላሙን ያድለን፤ አሜን።
[[መደብ:ክርስትና]]
[[መደብ:ክርስትና]]

እትም በ23:00, 26 ጃንዩዌሪ 2022

የንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት በአብዛኞቹ አብያተ ክርስቲያናት የሚቀበል የክርስትና እምነት መግለጫ ነው።

እንዲያውም የዛሬው ጸሎት ከንቅያ ጉባኤ በኋላ፣ በቁስጥንጥንያ ጉባኤ የተዘጋጀው ነው። ሁለተኛው ጉባኤ አንዳንድ ቃላት በተለይም ስለ መንፈስ ቅዱስ በይበልጥ የሚገለጽ ቋንቋ ጨመረ። በመጀመርያውም እትም፣ መጨረሻው ዓረፍተ ነገር ሀረ ጤቆች ይወገዙ ይል ነበር፤ በዚህ ፈንታ አዲሱ ጸሎተ ሃይማኖት የጥምቀትየሙታን ትንሳኤና ዘላለም ሕይወት እምነቶች ይጠቅሳል።

ከ372 ዓም ጀምሮ እስካሁን በምንም ሳይቀየር በተዋሕዶምሥራቅ ኦርቶዶክስሮማን ካቶሊክፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያን ሁሉ በሙሉ ይቀበላል። ሞርሞኖች ወይም የይሆዋ ምሥክሮች ግን ሥላሴን የማይቀበሉ እምነቶች ናቸው።

የሃይማኖት ጸሎት (የተሻለው 372 ዓ.ም. ቁስጥንጥንያ እንደ ተዘጋጀ)

ኹሉን በያዘ፣ ሰማይንና ምድርን፥ የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ፡ አንድ አምላክ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን።

ዓለም ሳይፈጠር፡ ከእርሱ ጋራ በነበረ፥ አንድ የአብ ልጅ፥ አንድ ጌታ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር ወልድም እናምናለን። እርሱም፡ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን፥ ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ፥ የተወለደ እንጂ፡ ያልተፈጠረ፣ በመለኮቱ፡ ከአብ ጋራ የሚተካከል፣ ኹሉ፡ በእርሱ የኾነው፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በሰማይ ካለው፣ በምድርም ካለው፡ ያለእርሱ፡ ምንም ምን፡ የኾነ የለም።

ስለእኛ ስለሰዎች፥ እኛን ለማዳን፡ ከሰማይ ወረደ፤ በመንፈስ ቅዱስ ግብር፡ ከቅድስት ድንግል ማርያም፡ ከሥጋዋ፡ ሥጋ፥ ከነፍሷ፡ ነፍስ ነሥቶ፡ ፍጹም ሰውን ኾነ። በጴንጤናዊው ጲላጦስ ዘመን፡ ስለእኛ፡ መከራን ተቀበለ። ተሰቀለ። ሞተ። ተቀበረ። በሦስተኛውም ቀን፡ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ። በክብር፥ በምስጋና፡ ወደሰማይ ዐረገ። በአባቱም ቀኝ፡ በዙፋኑ ተቀመጠ። ዳግመኛም፡ በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ፡ በምስጋና ይመለሳል። ለመንግሥቱ፡ ፍጻሜ የለውም።

በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም እናምናለን። እርሱም፡ ሕይወትን የሚሰጥ፣ ከአብ የሠረፀና በነቢያት ዐድሮ የተናገረው፥ በሓዋርያት ላይ የወረደውና በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት፡ ዓለሙን፡ በጸጋው የሞላው፡ ቅዱሱ የእውነት መንፈስ ነው። ለእርሱም፡ ከአብና ከወልድ ጋራ፡ በአንድነት እንሰግድለታለን፤ እናመሰግነዋለንም።

በአንዲት ቅድስት ካቶሊክ እና ሐዋርያዊት[1] ቤተ ክርስቲያን እናምናለን።

ኃጢኣት በሚሠረይባት፡ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን።

በሙታን ትንሣኤ፥ በዘለዓለምም ሕይወት እናምናለን። ለዘለዓለሙ፤ አሜን።

በመጀመርያው ንቅያ ጉባኤ በ317 ዓ.ም. እንደ ተጻፈ

ኹሉን በያዘ፣ የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ፡ አንድ አምላክ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን።

ከእርሱ ጋራ በነበረ፥ የአብ ልጅ፥ አንድ ጌታ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር ወልድም እናምናለን። እርሱም፡ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን፥ ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ፥ የተወለደ እንጂ፡ ያልተፈጠረ፣ በመለኮቱ፡ ከአብ ጋራ የሚተካከል፣ ኹሉ፡ በእርሱ የኾነው፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በሰማይ ካለው፣ በምድርም ካለው፡ ያለእርሱ፡ ምንም ምን፡ የኾነ የለም።

ስለእኛ ስለሰዎች፥ እኛን ለማዳን፡ ወረደ፤ ነፍስ ነሥቶ፡ ፍጹም ሰውን ኾነ። መከራን ተቀበለ። በሦስተኛውም ቀን፡ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ። ወደሰማይ ዐረገ። ዳግመኛም፡ በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ፡ ይመለሳል።

በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም እናምናለን።

ነገር ግን፣ «ያልተገኘበት ዘመን ነበር» እና «ሳይፈጠር አልነበረም» እና «ከአንዳችም ተፈጠረ»፣ ወይም «ከሌላ ባሕርይ ነው» ወይም «የእግዚአብሔር ወልድ ይፈጠራል» ወይም «የሚለወጥ ነው» የሚሉት፦ በቅድሥት ካቶሊክ እና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን ዘንድ ይወገዙ።

ዋቢ ምንጭ

  1. ^ በኢ.ኦ.ተ.ቤ አገልግሎት በተጨማሪ እንዲህ ይላል፦ «ኢየሱስ ክርስቶስ፡ ጥንት፡ በቀደሙት ሰዎች ኪዳነ ልቦና በመሠረታት፥ በነቢያት ቃል ባጸናትና በሓዋርያት ጕባኤ በፈጸማት፥ ካህናት፡ የእርሱን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም፡ ለመሥዋዕትነት በሚያቀርቡባት፥ ምእመናንና ምእመናትም፡ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋዎች በሚቀበሉባት፡ በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን።» ጸሎተ ሃይማኖት በግዕዝና በአማርኛ