ከ«የንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
Fixed typo
Tags: በንፋስ ስልክ Mobile app edit iOS app edit
Fixed typo
Tags: በንፋስ ስልክ Mobile app edit iOS app edit
መስመር፡ 1፦ መስመር፡ 1፦
{{infobox|abovestyle=background:#FFBF00|above='''የንቅያ የሃይሚኖት ፀሎት'''
{{infobox|abovestyle=background:#FFBF00|above='''የንቅያ የሃይሚኖት ፀሎት'''
|image=[[File:Nicaea icon.jpg|223px|thumb|center|የንቅያ ጉባዔ ተሳታፊዎች በመዐከል ፃድቁ ቅዱስ ቆጠጢኖስ]]
|image=[[File:Nicaea icon.jpg|223px|thumb|center|የንቅያ ጉባዔ ተሳታፊዎች በመዐከል ፃድቁ ንጉሥ ቅዱስ ቆጠጢኖስ]]
|caption=|headerstyle=background:#FFBF00|header1=የክርስትና እምነት መግለጫ የተመሠረተበት ጉባዔ|headerstyle=background:#FFBF00|header8=<span style="color:#FFBF00">
|caption=|headerstyle=background:#FFBF00|header1=የክርስትና እምነት መግለጫ የተመሠረተበት ጉባዔ|headerstyle=background:#FFBF00|header8=<span style="color:#FFBF00">
</span>|label1=|data1=|label2=ሰብሳቢ|data2=ፃድቁ ንጉሥ ቆስጥንጢኖስ |label3=የተወሰነበት ቀን|data3=፫የ፸፪ ዓ.ም|label4=የተሰበሰቡት ሊቃነ አበው ብዛት|data4=፫የ፲፰ ሊቃነ አበው|label5=ቦታው|data5=በንቅያ ቁስጥንጥኒያ|label6=የሚከበርበት ቀን|data6=[[ኅዳር ፱]] ቀን በመላው ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን|label7=|data7=|captionstyle=|header5=}}
</span>|label1=|data1=|label2=ሰብሳቢ|data2=ፃድቁ ንጉሥ ቆስጥንጢኖስ |label3=የተወሰነበት ቀን|data3=፫የ፸፪ ዓ.ም|label4=የተሰበሰቡት ሊቃነ አበው ብዛት|data4=፫የ፲፰ ሊቃነ አበው|label5=ቦታው|data5=በንቅያ ቁስጥንጥኒያ|label6=የሚከበርበት ቀን|data6=[[ኅዳር ፱]] ቀን በመላው ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን|label7=|data7=|captionstyle=|header5=}}

እትም በ01:15, 19 ማርች 2022

የንቅያ የሃይሚኖት ፀሎት
የንቅያ ጉባዔ ተሳታፊዎች በመዐከል ፃድቁ ንጉሥ ቅዱስ ቆጠጢኖስ
የክርስትና እምነት መግለጫ የተመሠረተበት ጉባዔ
ሰብሳቢ ፃድቁ ንጉሥ ቆስጥንጢኖስ
የተወሰነበት ቀን ፫የ፸፪ ዓ.ም
የተሰበሰቡት ሊቃነ አበው ብዛት ፫የ፲፰ ሊቃነ አበው
ቦታው በንቅያ ቁስጥንጥኒያ
የሚከበርበት ቀን ኅዳር ፱ ቀን በመላው ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን


የንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት በአብዛኞቹ አብያተ ክርስቲያናት የሚቀበል የክርስትና እምነት መግለጫ ነው።

እንዲያውም የዛሬው ጸሎት ከንቅያ ጉባኤ በኋላ፣ በቁስጥንጥንያ ጉባኤ የተዘጋጀው ነው። ሁለተኛው ጉባኤ አንዳንድ ቃላት በተለይም ስለ መንፈስ ቅዱስ በይበልጥ የሚገለጽ ቋንቋ ጨመረ። በመጀመርያውም እትም፣ መጨረሻው ዓረፍተ ነገር ሀረ ጤቆች ይወገዙ ይል ነበር፤ በዚህ ፈንታ አዲሱ ጸሎተ ሃይማኖት የጥምቀትየሙታን ትንሳኤና ዘላለም ሕይወት እምነቶች ይጠቅሳል።

ከ372 ዓም ጀምሮ እስካሁን በምንም ሳይቀየር በተዋሕዶምሥራቅ ኦርቶዶክስሮማን ካቶሊክፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያን ሁሉ በሙሉ ይቀበላል። ሞርሞኖች ወይም የይሆዋ ምሥክሮች ግን ሥላሴን የማይቀበሉ እምነቶች ናቸው።

የሃይማኖት ጸሎት (የተሻለው 372 ዓ.ም. ቁስጥንጥንያ እንደ ተዘጋጀ)

ኹሉን በያዘ፣ ሰማይንና ምድርን፥ የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ፡ አንድ አምላክ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን።

ዓለም ሳይፈጠር፡ ከእርሱ ጋራ በነበረ፥ አንድ የአብ ልጅ፥ አንድ ጌታ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር ወልድም እናምናለን። እርሱም፡ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን፥ ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ፥ የተወለደ እንጂ፡ ያልተፈጠረ፣ በመለኮቱ፡ ከአብ ጋራ የሚተካከል፣ ኹሉ፡ በእርሱ የኾነው፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በሰማይ ካለው፣ በምድርም ካለው፡ ያለእርሱ፡ ምንም ምን፡ የኾነ የለም።

ስለእኛ ስለሰዎች፥ እኛን ለማዳን፡ ከሰማይ ወረደ፤ በመንፈስ ቅዱስ ግብር፡ ከቅድስት ድንግል ማርያም፡ ከሥጋዋ፡ ሥጋ፥ ከነፍሷ፡ ነፍስ ነሥቶ፡ ፍጹም ሰውን ኾነ። በጴንጤናዊው ጲላጦስ ዘመን፡ ስለእኛ፡ መከራን ተቀበለ። ተሰቀለ። ሞተ። ተቀበረ። በሦስተኛውም ቀን፡ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ። በክብር፥ በምስጋና፡ ወደሰማይ ዐረገ። በአባቱም ቀኝ፡ በዙፋኑ ተቀመጠ። ዳግመኛም፡ በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ፡ በምስጋና ይመለሳል። ለመንግሥቱ፡ ፍጻሜ የለውም።

በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም እናምናለን። እርሱም፡ ሕይወትን የሚሰጥ፣ ከአብ የሠረፀና በነቢያት ዐድሮ የተናገረው፥ በሓዋርያት ላይ የወረደውና በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት፡ ዓለሙን፡ በጸጋው የሞላው፡ ቅዱሱ የእውነት መንፈስ ነው። ለእርሱም፡ ከአብና ከወልድ ጋራ፡ በአንድነት እንሰግድለታለን፤ እናመሰግነዋለንም።

በአንዲት ቅድስት ካቶሊክ እና ሐዋርያዊት[1] ቤተ ክርስቲያን እናምናለን።

ኃጢኣት በሚሠረይባት፡ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን።

በሙታን ትንሣኤ፥ በዘለዓለምም ሕይወት እናምናለን። ለዘለዓለሙ፤ አሜን።

በመጀመርያው ንቅያ ጉባኤ በ317 ዓ.ም. እንደ ተጻፈ

ኹሉን በያዘ፣ የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ፡ አንድ አምላክ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን።

ከእርሱ ጋራ በነበረ፥ የአብ ልጅ፥ አንድ ጌታ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር ወልድም እናምናለን። እርሱም፡ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን፥ ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ፥ የተወለደ እንጂ፡ ያልተፈጠረ፣ በመለኮቱ፡ ከአብ ጋራ የሚተካከል፣ ኹሉ፡ በእርሱ የኾነው፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በሰማይ ካለው፣ በምድርም ካለው፡ ያለእርሱ፡ ምንም ምን፡ የኾነ የለም።

ስለእኛ ስለሰዎች፥ እኛን ለማዳን፡ ወረደ፤ ነፍስ ነሥቶ፡ ፍጹም ሰውን ኾነ። መከራን ተቀበለ። በሦስተኛውም ቀን፡ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ። ወደሰማይ ዐረገ። ዳግመኛም፡ በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ፡ ይመለሳል።

በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም እናምናለን።

ነገር ግን፣ «ያልተገኘበት ዘመን ነበር» እና «ሳይፈጠር አልነበረም» እና «ከአንዳችም ተፈጠረ»፣ ወይም «ከሌላ ባሕርይ ነው» ወይም «የእግዚአብሔር ወልድ ይፈጠራል» ወይም «የሚለወጥ ነው» የሚሉት፦ በቅድሥት ካቶሊክ እና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን ዘንድ ይወገዙ።

ዋቢ ምንጭ

  1. ^ በኢ.ኦ.ተ.ቤ አገልግሎት በተጨማሪ እንዲህ ይላል፦ «ኢየሱስ ክርስቶስ፡ ጥንት፡ በቀደሙት ሰዎች ኪዳነ ልቦና በመሠረታት፥ በነቢያት ቃል ባጸናትና በሓዋርያት ጕባኤ በፈጸማት፥ ካህናት፡ የእርሱን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም፡ ለመሥዋዕትነት በሚያቀርቡባት፥ ምእመናንና ምእመናትም፡ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋዎች በሚቀበሉባት፡ በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን።» ጸሎተ ሃይማኖት በግዕዝና በአማርኛ