ከ«ኢትዮጵያ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 46፦ መስመር፡ 46፦


== ታሪክ ==
== ታሪክ ==
የአክሱም መንግሥት የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥት ነበር። ከፐርሺያ ፣ ሮም እና ቻይና ጋር የጊዜው ትልቅ ኅይል ይባል ነበር። በ6ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን አክሱም የአሁኑን የመን ይቆጣጠር ነበር። በ1270 እ.ኤ.አ. የሰለሞን መንግሥት ኢትዮጵያን መቆጣጠር ጀመረ።

በ1880ዎቹ እ.ኤ.አ፞የአውሮፓ መንግሥቶች አፍሪካን በቅኝ መግዛት ጀመሩ። 1896 እ.ኤ.አ. በኢትዮጵያ እና ጣልያን መካከል የነበሩ ውዝግቦች ወደ አድዋ ጦርነት መሩ። በዚህም ጊዜ የጣልያን ትልቅ ጦር በማሸነፍ ዓለምን አስደነቁ።

በ20ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ኢትዮጵያን መምራት ጀመሩ።

*[[አክሱም]]
*[[አክሱም]]
*[[ላሊበላ]]
*[[ላሊበላ]]

እትም በ04:52, 28 ዲሴምበር 2005

የኢትዮጵያ ፈደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
Flag of Ethiopia Ethiopia COA
የኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ የኢትዮጵያ ብሄራዊ አርማ
Location of Ethiopia
ብሔራዊ ቋንቋ አማርኛ
ዋና ከተማ አዲስ አበባ
ፕሬዝዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ
የመሬት ስፋት 1,127,127 ካሬ ኪ.ሜ. (ከዓለም 26ኛ)
የህዝብ ብዛት 73,053,286 (ከዓለም 16ኛ)
ገንዘብ ብር
ብሄራዊ መዝሙር ወደፊት ገስግሺ ውድ እናት ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያኣፍሪካ ቀንድ የምትገኝ የረጅም ዘመን ታሪክ ያላት ኣገር ናት። ድሮ ኣቢሲኒያ ተብላ ትታወቅ የነበረ ሲሆን በአፍሪካ ነፃነታቸውን አስጠብቀው ለመኖር ከቻሉ ሁለት አገሮች አንዷ ነች። የዘመኑ የታሪክ መርማሪዎች ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ከግሪክ የወጣና ትርጉሙም "በፀሃይ የጠቆረ መልክ" ማለት ነው ይላሉ። ቀደምት ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ግን ይህን ሳይቀበሉ ስያሜው የአክሱም መስራች ከሆነው "ኢትዮጲስ" ከተባለው የኩሽ ልጅ (የካም ልጅ፣ የኖህ የልጅ ልጅ) የተወሰደ ነው ይላሉ።


ታሪክ

የአክሱም መንግሥት የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥት ነበር። ከፐርሺያ ፣ ሮም እና ቻይና ጋር የጊዜው ትልቅ ኅይል ይባል ነበር። በ6ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን አክሱም የአሁኑን የመን ይቆጣጠር ነበር። በ1270 እ.ኤ.አ. የሰለሞን መንግሥት ኢትዮጵያን መቆጣጠር ጀመረ።

በ1880ዎቹ እ.ኤ.አ፞የአውሮፓ መንግሥቶች አፍሪካን በቅኝ መግዛት ጀመሩ። 1896 እ.ኤ.አ. በኢትዮጵያ እና ጣልያን መካከል የነበሩ ውዝግቦች ወደ አድዋ ጦርነት መሩ። በዚህም ጊዜ የጣልያን ትልቅ ጦር በማሸነፍ ዓለምን አስደነቁ።

በ20ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ኢትዮጵያን መምራት ጀመሩ።

ሥነ-መንግስት

መልክዓ-ምድር

ኢትዮጵያ በሰሜን ምስራቅ አፍረካ በ8 ዲግሪ ኬክሮስ እና በ39 ዲግሪ ኬንትሮስ ላይ የምትገኝ አገር ስትሆን የቆዳ ስፋቱዋም 1,127,127 ካሬ ኪ.ሜ ነው። በሰሜን ከኤርትራ፣ በምዕራብ ከሱዳን፣ በደቡብ ከኬኒያ፣ እንዲሁም በምስራቅ ከጅቡቲ እና ከሶማሊያ ጋር ትዋሰናለች። ኢትዮጵያ በአብዛኛው ተራሮችና አንባዎች የሞሉዋት አገር ስተሆን ታላቁ የምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ እነዚህኑ ከፍተኛ ቦታዎች ከሰሜን ምስራቅ ወደ ደቡብ ምዕራብ በመክፈል ያልፋል። በስምጥ ሸለቆው ዙሪያም በረሃማ የሆኑ ዝቅተኛ ቦታዎች ይገኛሉ። ይሄን መሰሉ የመልክዓ-ምድር ልዩነት አገሪትዋ የተለያየ የዓየር-ንብረት፣ አፈር፣ እፅዋት እና የህዝብ አሰፋፈር እንዲኖራት አስችሏል። በከፍታና በመልክዓምድራዊ አቀማመጥ መሰረት በኢትዮጵያ ውስጥ ሶስት አይነት ዓየርንብረታዊ ክልሎች የሚገኙ ሲሆን እነርሱም፦

  • ደጋ - ከባህር ወለል በላይ 2400 ሜትር እና ከዚያ በላይ የሆኑ አካባቢዎች ሲሆኑ የሙቀት መጠናቸውም እስከ 16 ዲግረ ሴ.ግ፣
  • ወይናደጋ - ከባህር ወለል በላይ ከ1500 እስከ 2400 ሜትር ከፍታ ያላቸውና ሙቀታቸውም ከ16 ዲግረ ሴ.ግ እስከ 30 ዲግረ ሴ.ግ፣ እና
  • ቆላ - ከባህር ወለል በላይ 1500 ሜትር እና ከዛም በታች ከፍታ ያላቸው አከባቢዎች ሲሆኑ የሙቀት መጠናቸውም ከ30 ዲግረ ሴ.ግ እስከ 50 ዲግረ ሴ.ግ ናቸው።

መደበኛው የዝናብ ወቅት ከሰኔ አጋማሽ እስከ መስከረም አጋማሽ ሲሆን እርሱንም ተከትሎ አልፎ አልፎ የሚጥል ዝናብ በየካቲት እና በመጋቢት ይከሰታል። የተቀሩት ወራት በአብዛኛው ደረቅ ናቸው።

አስተዳደራዊ ክልሎች

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጽያ ውስጥ 9 አስተዳደራዊ ክልሎች ይገኛሉ። አወቃቀራቸውም በህገመንግስቱ በተደነገገው መሰረት "በህዝብ አሰፋፈር፤ ቋንቋ፤ ማንነት እና ፈቃድ ላይ" ተመስርቶ ሲሆን ክልሎቹም ፦


ህዝብ

ኢትዮጵያ ከ80 በላይ የሚሆኑ ብሄረሰቦች የሚገኙባት "የብሄረሰቦች ሙዚየም" ልትሰኝ የምተችል አገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች የኦሮሞ፣ የአማራ፣ እና የትግሬ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የአገሪቱዋ ህዝብ ቁጥር 3/4ኛ የሚሆነውን ይይዛሉ።

ቋንቋዎች

በኢትዮጵያ ውስጥ ከ80 በላይ ብሄር ብሄረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ80 በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት፡፡ በአሁኑ ወቅት በእብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የብሄራዊ ቋንቋ ነው፡፡ በኢትዮጵያ የሚነገሩት ቋንቋዎች ወደ አራት ዋና ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሌ። እነዚሁም

  • ኩሻዊ፦ ወደ 19 ቋንቋዎችን የያዘ
  • የአባይ-ሰሃራዊ፦ወደ 20 ቋንቋዎችን የያዘ
  • ኦሞአዊ፦ወደ 23 ቋንቋዎችን የያዘ እና
  • ሴማዊ፦ወደ 12 ቋንቋዎች የያዘ ናቸው።

ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ ኦሮምኛ፣ ሶማሊኛ፣ አፋርኛ፣ ሲዳምኛ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ፣ ኩናማኛ፣ ጉሙዝኛ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። እንደ ወላይትኛ፣ ጋሞኛ፣ ከፋኛ፣ ሃመርኛ የመሳሰሉት የኦሞአዊ ቋንቋ ዘሮች ሲሆኑ አማርኛ፣ ትግርኛ፣ ጉራጊኛ፣ ስልጢኛ፣ ሀደሪኛ እና መሰል ቋንቋዎች ከሴማዊ ቋነቋዎች ይመደባሉ።
የሴሚቲክ ምንጭ ያላቸው እንደ አማርኛ ያሉት ቋንቋዎች የራሱ የሆነ የተለየ የፊደል ስርአት ያላቸው ሲሆን ይህም ኢትዮጵያን ከአፍሪቃ ብቸኛዋ ባለ ፊደል ሀገር ያደርጋታል፡፡ እነኚህ የሴሚቲክ ምንጭ ያላችው ቋንቋዎች ግዕዝ የተባለ በአሁኑ ወቅት ከቤተክርስትያን ውጭ ለእለት ተእለት ግልጋሎት ላይ የማይውል ግንድ ዘር አላቸው፡፡

ምጣኔ-ሃብት

ባህል እና ሃይማኖት

የህዝብ በዓላት (የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የሚለውንም ተመልከት)
ቀን የበዓሉ ስም የበዓሉ ስም በእንግሊዝኛ አስተያየት
መስከረም ፩ እንቁጣጣሽ Ethiopian New Year  
መስከረም ፲፯ መስቀል Finding of the True Cross  
ጥቅምት ፳፬ ኢድ አል ፈጥር End of Ramadan ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም ነው
ታህሳስ ፳፱ ገና Christmas  
ጥር ፪ ኢድ አል አደሃ Eid ul-Adha (Feast of the Sacrifice) ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም ነው
ጥር ፲፩ ጥምቀት Epiphany  
የካቲት ፳፫ የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል Battle of Adowa Commemoration Day  
ሚያዚያ ፬ መውሊድ (የነብዩ መሃመድ የልደት ቀን) Birthday of The Prophet Muhammad ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም ነው
ሚያዚያ ፲፫ ስቅለት Good Friday (Crucifixion) ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም ነው
ሚያዚያ ፲፭ ትንሳዔ (ፋሲካ) Easter ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም ነው
ሚያዚያ ፳፯ የጀግኖች አርበኞች መታሰቢያ ቀን Patriots' Day  
ግንቦት ፳ ደርግ የወደቀበት ቀን Downfall of the Duerg Regime  



ኢትዮጵያ

ታሪካዊ ቦታዎች - አክሱም | ላሊበላ | ጎንደር | ነጋሽ | ሐረር | ደብረ-ዳሞ | አዲስ አበባ
አስተዳደራዊ ክልሎች - ትግራይ | አፋር | አማራ | ኦሮሚያ | ሶማሌ | ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል | ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች | ጋምቤላ | ሐረሪ | አዲስ አበባ | ድሬዳዋ
ቋንቋዎች - አማርኛ | ግዕዝ | ኦሮምኛ | ትግርኛ | ጉራጊኛ | ሶማሊኛ | አፋርኛ | ሲዳምኛ | ሃዲያኛ | ከምባትኛ | ወላይትኛ | ጋሞኛ | ከፋኛ | ሃመርኛ | ስልጢኛ | ሀደሪኛ
መልክዓ-ምድር - አባይ | አዋሽ | ራስ-ዳሽን | ሶፍ-ዑመር | ጣና | ደንከል | ላንጋኖ | አቢያታ | ሻላ
ከተሞች - የኢትዮጵያ ከተሞች