ከ«ኢትዮጵያ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
ጥNo edit summary |
|||
መስመር፡ 46፦ | መስመር፡ 46፦ | ||
== ታሪክ == |
== ታሪክ == |
||
የአክሱም መንግሥት የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥት ነበር። ከፐርሺያ ፣ ሮም እና ቻይና ጋር የጊዜው ትልቅ ኅይል ይባል ነበር። በ6ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን አክሱም የአሁኑን የመን ይቆጣጠር ነበር። በ1270 እ.ኤ.አ. የሰለሞን መንግሥት ኢትዮጵያን መቆጣጠር ጀመረ። |
|||
በ1880ዎቹ እ.ኤ.አ፞የአውሮፓ መንግሥቶች አፍሪካን በቅኝ መግዛት ጀመሩ። 1896 እ.ኤ.አ. በኢትዮጵያ እና ጣልያን መካከል የነበሩ ውዝግቦች ወደ አድዋ ጦርነት መሩ። በዚህም ጊዜ የጣልያን ትልቅ ጦር በማሸነፍ ዓለምን አስደነቁ። |
|||
በ20ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ኢትዮጵያን መምራት ጀመሩ። |
|||
*[[አክሱም]] |
*[[አክሱም]] |
||
*[[ላሊበላ]] |
*[[ላሊበላ]] |
እትም በ04:52, 28 ዲሴምበር 2005
| |||||
ብሔራዊ ቋንቋ | አማርኛ | ||||
ዋና ከተማ | አዲስ አበባ | ||||
ፕሬዝዳንት | ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ | ||||
ጠቅላይ ሚኒስትር | መለስ ዜናዊ | ||||
የመሬት ስፋት | 1,127,127 ካሬ ኪ.ሜ. (ከዓለም 26ኛ) | ||||
የህዝብ ብዛት | 73,053,286 (ከዓለም 16ኛ) | ||||
ገንዘብ | ብር | ||||
ብሄራዊ መዝሙር | ወደፊት ገስግሺ ውድ እናት ኢትዮጵያ |
ኢትዮጵያ በኣፍሪካ ቀንድ የምትገኝ የረጅም ዘመን ታሪክ ያላት ኣገር ናት። ድሮ ኣቢሲኒያ ተብላ ትታወቅ የነበረ ሲሆን በአፍሪካ ነፃነታቸውን አስጠብቀው ለመኖር ከቻሉ ሁለት አገሮች አንዷ ነች። የዘመኑ የታሪክ መርማሪዎች ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ከግሪክ የወጣና ትርጉሙም "በፀሃይ የጠቆረ መልክ" ማለት ነው ይላሉ። ቀደምት ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ግን ይህን ሳይቀበሉ ስያሜው የአክሱም መስራች ከሆነው "ኢትዮጲስ" ከተባለው የኩሽ ልጅ (የካም ልጅ፣ የኖህ የልጅ ልጅ) የተወሰደ ነው ይላሉ።
ታሪክ
የአክሱም መንግሥት የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥት ነበር። ከፐርሺያ ፣ ሮም እና ቻይና ጋር የጊዜው ትልቅ ኅይል ይባል ነበር። በ6ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን አክሱም የአሁኑን የመን ይቆጣጠር ነበር። በ1270 እ.ኤ.አ. የሰለሞን መንግሥት ኢትዮጵያን መቆጣጠር ጀመረ።
በ1880ዎቹ እ.ኤ.አ፞የአውሮፓ መንግሥቶች አፍሪካን በቅኝ መግዛት ጀመሩ። 1896 እ.ኤ.አ. በኢትዮጵያ እና ጣልያን መካከል የነበሩ ውዝግቦች ወደ አድዋ ጦርነት መሩ። በዚህም ጊዜ የጣልያን ትልቅ ጦር በማሸነፍ ዓለምን አስደነቁ።
በ20ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ኢትዮጵያን መምራት ጀመሩ።
ሥነ-መንግስት
መልክዓ-ምድር
ኢትዮጵያ በሰሜን ምስራቅ አፍረካ በ8 ዲግሪ ኬክሮስ እና በ39 ዲግሪ ኬንትሮስ ላይ የምትገኝ አገር ስትሆን የቆዳ ስፋቱዋም 1,127,127 ካሬ ኪ.ሜ ነው። በሰሜን ከኤርትራ፣ በምዕራብ ከሱዳን፣ በደቡብ ከኬኒያ፣ እንዲሁም በምስራቅ ከጅቡቲ እና ከሶማሊያ ጋር ትዋሰናለች። ኢትዮጵያ በአብዛኛው ተራሮችና አንባዎች የሞሉዋት አገር ስተሆን ታላቁ የምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ እነዚህኑ ከፍተኛ ቦታዎች ከሰሜን ምስራቅ ወደ ደቡብ ምዕራብ በመክፈል ያልፋል። በስምጥ ሸለቆው ዙሪያም በረሃማ የሆኑ ዝቅተኛ ቦታዎች ይገኛሉ። ይሄን መሰሉ የመልክዓ-ምድር ልዩነት አገሪትዋ የተለያየ የዓየር-ንብረት፣ አፈር፣ እፅዋት እና የህዝብ አሰፋፈር እንዲኖራት አስችሏል። በከፍታና በመልክዓምድራዊ አቀማመጥ መሰረት በኢትዮጵያ ውስጥ ሶስት አይነት ዓየርንብረታዊ ክልሎች የሚገኙ ሲሆን እነርሱም፦
- ደጋ - ከባህር ወለል በላይ 2400 ሜትር እና ከዚያ በላይ የሆኑ አካባቢዎች ሲሆኑ የሙቀት መጠናቸውም እስከ 16 ዲግረ ሴ.ግ፣
- ወይናደጋ - ከባህር ወለል በላይ ከ1500 እስከ 2400 ሜትር ከፍታ ያላቸውና ሙቀታቸውም ከ16 ዲግረ ሴ.ግ እስከ 30 ዲግረ ሴ.ግ፣ እና
- ቆላ - ከባህር ወለል በላይ 1500 ሜትር እና ከዛም በታች ከፍታ ያላቸው አከባቢዎች ሲሆኑ የሙቀት መጠናቸውም ከ30 ዲግረ ሴ.ግ እስከ 50 ዲግረ ሴ.ግ ናቸው።
መደበኛው የዝናብ ወቅት ከሰኔ አጋማሽ እስከ መስከረም አጋማሽ ሲሆን እርሱንም ተከትሎ አልፎ አልፎ የሚጥል ዝናብ በየካቲት እና በመጋቢት ይከሰታል። የተቀሩት ወራት በአብዛኛው ደረቅ ናቸው።
አስተዳደራዊ ክልሎች
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጽያ ውስጥ 9 አስተዳደራዊ ክልሎች ይገኛሉ። አወቃቀራቸውም በህገመንግስቱ በተደነገገው መሰረት "በህዝብ አሰፋፈር፤ ቋንቋ፤ ማንነት እና ፈቃድ ላይ" ተመስርቶ ሲሆን ክልሎቹም ፦
- የትግራይ ክልል
- የአፋር ክልል
- የአማራ ክልል
- የኦሮሚያ ክልል
- የሶማሌ ክልል
- የቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል
- የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል
- የጋምቤላ ሕዝቦች ክልል
- የሀረሪ ሕዝብ ክልል ሲሆኑ በተጨማሪም
- አዲስ አበባ እና
- ድሬዳዋ እራሳቸውን የቻሉ የአስተዳደር አካባቢዎች ሆነው ተዋቅረዋል።
ህዝብ
ኢትዮጵያ ከ80 በላይ የሚሆኑ ብሄረሰቦች የሚገኙባት "የብሄረሰቦች ሙዚየም" ልትሰኝ የምተችል አገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች የኦሮሞ፣ የአማራ፣ እና የትግሬ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የአገሪቱዋ ህዝብ ቁጥር 3/4ኛ የሚሆነውን ይይዛሉ።
ቋንቋዎች
በኢትዮጵያ ውስጥ ከ80 በላይ ብሄር ብሄረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ80 በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት፡፡ በአሁኑ ወቅት በእብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የብሄራዊ ቋንቋ ነው፡፡ በኢትዮጵያ የሚነገሩት ቋንቋዎች ወደ አራት ዋና ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሌ። እነዚሁም
- ኩሻዊ፦ ወደ 19 ቋንቋዎችን የያዘ
- የአባይ-ሰሃራዊ፦ወደ 20 ቋንቋዎችን የያዘ
- ኦሞአዊ፦ወደ 23 ቋንቋዎችን የያዘ እና
- ሴማዊ፦ወደ 12 ቋንቋዎች የያዘ ናቸው።
ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ ኦሮምኛ፣ ሶማሊኛ፣ አፋርኛ፣ ሲዳምኛ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ፣ ኩናማኛ፣ ጉሙዝኛ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። እንደ ወላይትኛ፣ ጋሞኛ፣ ከፋኛ፣ ሃመርኛ የመሳሰሉት የኦሞአዊ ቋንቋ ዘሮች ሲሆኑ አማርኛ፣ ትግርኛ፣ ጉራጊኛ፣ ስልጢኛ፣ ሀደሪኛ እና መሰል ቋንቋዎች ከሴማዊ ቋነቋዎች ይመደባሉ።
የሴሚቲክ ምንጭ ያላቸው እንደ አማርኛ ያሉት ቋንቋዎች የራሱ የሆነ የተለየ የፊደል ስርአት ያላቸው ሲሆን ይህም ኢትዮጵያን ከአፍሪቃ ብቸኛዋ ባለ ፊደል ሀገር ያደርጋታል፡፡ እነኚህ የሴሚቲክ ምንጭ ያላችው ቋንቋዎች ግዕዝ የተባለ በአሁኑ ወቅት ከቤተክርስትያን ውጭ ለእለት ተእለት ግልጋሎት ላይ የማይውል ግንድ ዘር አላቸው፡፡
ምጣኔ-ሃብት
ባህል እና ሃይማኖት
ቀን | የበዓሉ ስም | የበዓሉ ስም በእንግሊዝኛ | አስተያየት |
---|---|---|---|
መስከረም ፩ | እንቁጣጣሽ | Ethiopian New Year | |
መስከረም ፲፯ | መስቀል | Finding of the True Cross | |
ጥቅምት ፳፬ | ኢድ አል ፈጥር | End of Ramadan | ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም ነው |
ታህሳስ ፳፱ | ገና | Christmas | |
ጥር ፪ | ኢድ አል አደሃ | Eid ul-Adha (Feast of the Sacrifice) | ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም ነው |
ጥር ፲፩ | ጥምቀት | Epiphany | |
የካቲት ፳፫ | የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል | Battle of Adowa Commemoration Day | |
ሚያዚያ ፬ | መውሊድ (የነብዩ መሃመድ የልደት ቀን) | Birthday of The Prophet Muhammad | ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም ነው |
ሚያዚያ ፲፫ | ስቅለት | Good Friday (Crucifixion) | ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም ነው |
ሚያዚያ ፲፭ | ትንሳዔ (ፋሲካ) | Easter | ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም ነው |
ሚያዚያ ፳፯ | የጀግኖች አርበኞች መታሰቢያ ቀን | Patriots' Day | |
ግንቦት ፳ | ደርግ የወደቀበት ቀን | Downfall of the Duerg Regime |
ኢትዮጵያ |
ታሪካዊ ቦታዎች - አክሱም | ላሊበላ | ጎንደር | ነጋሽ | ሐረር | ደብረ-ዳሞ | አዲስ አበባ |
|