ከ«ኢትዮጵያ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
adding commons template
robot Adding: stq:Äthiopien
መስመር፡ 288፦ መስመር፡ 288፦
[[sq:Etiopia]]
[[sq:Etiopia]]
[[sr:Етиопија]]
[[sr:Етиопија]]
[[stq:Äthiopien]]
[[sv:Etiopien]]
[[sv:Etiopien]]
[[sw:Ethiopia]]
[[sw:Ethiopia]]

እትም በ16:49, 28 ጁላይ 2008

የኢትዮጵያ ፈደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
Flag of Ethiopia Ethiopia COA
የኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ የኢትዮጵያ ብሄራዊ አርማ
Location of Ethiopia
የሥራ ቋንቋ አማርኛ
ዋና ከተማ አዲስ አበባ
ፕሬዝዳንት መ/አለቃ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ
አፈ ጉባኤ አምባሰዳር ተሾመ ቶጋ
የመሬት ስፋት 1,127,127 ካሬ ኪ.ሜ. (ከዓለም 26ኛ)
የሕዝብ ብዛት 73,053,286 (ከዓለም 16ኛ)
ገንዘብ ብር
ብሔራዊ መዝሙር ወደፊት ገስግሺ ውድ እናት ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያኣፍሪካ ቀንድ የምትገኝ የረጅም ዘመን ታሪክ ያላት ሀገር ናት። ድሮ አቢሲኒያ በሚል መጠሪያ ትታወቅ ነበር። በአፍሪካ ነፃነታቸውን ጠብቀው ለመኖር ከቻሉ ሁለት አገሮች አንዷ ነች። የታሪክ ሊቃውንት ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ከግሪክ መወረሱን እና ትርጕሙም «በፀሓይ የከሰለ ገጽ» ማለት እንደሆነ ይገልጻሉ። ቀደምት የኢትዮጵያ ሊቃውንት ግን ይህን አይቀበሉትም። ስያሜው የአክሱም መሥራች ከነበረው «ኢትዮጲስ» እንደተገኘ፤ እርሱም የኩሽ ልጅ፣ (የካም የልጅ-ልጅ፣ የኖህ የልጅ-ልጅ-ልጅ) እንደነበር ይተርካሉ።

ታሪክ

የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቈጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ6ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቍጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ7ኛው እና በ8ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሣ በድንገት ሲያበቃ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ1262 ዓ.ም. ጨበጡ፤ እንዲያም ሲል የመጀመሪያው የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥት ዐፄ ሆኑ።

በ1880ዎቹ እ.ኤ.አ. የአውሮፓ መንግሥቶች አፍሪካን በቅኝ ገዢነት ማስተዳደር ጀመሩ። በኢትዮጵያ እና ጣልያን መካከል የነበሩ የዚያ ዘመን ውዝግቦች ወደ አድዋ ጦርነት በ1888 ዓ.ም. አመሩ። በጦርነቱ የጣልያን ትልቅ ዘመናዊ ጦር ትልቅ ሽንፈት የደረሰበት መሆኑ ዓለምን አስደነቁ።

በ20ኛው ምእት ሁለተኛው ሩብ ቀዳማዊ ኀይለ ሥላሴ ኢትዮጵያን መምራት ጀመሩ።

ሥነ-መንግሥት

መልክዓ-ምድር

ኢትዮጵያ በሰሜን ምስራቅ አፍረካ ከ3-14 ዲግሪ ሰሜን እና ከ33-48 ዲግሪ ምሥራቅ የምትገኝ አገር ስትሆን የቆዳ ስፋቱዋም 1,127,127 ካሬ ኪ.ሜ. ነው። በሰሜን ከኤርትራ፣ በምዕራብ ከሱዳን፣ በደቡብ ከኬኒያ፣ እንዲሁም በምሥራቅ ከጅቡቲ እና ከሶማሊያ ጋር ትዋሰናለች። የኢትዮጵያ አብዛኛው ግዛት በተራሮች እና አንባዎች የተሞላ ሲሆን፣ ታላቁ የምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ እነዚህኑ ከፍተኛ ቦታዎች ከሰሜን ምሥራቅ ወደ ደቡብ ምዕራብ በመጋደም ለሁለት ይከፍላቸዋል። በስምጥ ሸለቆው ዙሪያም በረሃማ የሆኑ ዝቅተኛ ቦታዎች ይገኛሉ። ይሄን መሰሉ የመልክዓ-ምድር ልዩነት አገሪቷ የተለያዩ የአየር ንብረት፣ የአፈር፣ የዕፅዋት እና የሕዝብ አሰፋፈር ገጽታዎች እንዲኖሯት አስችሏታል። በከፍታና በመልክዓምድራዊ አቀማመጥ የተነሣ በኢትዮጵያ ውስጥ ሦስት ዐይነት የአየርንብረት ክልሎች ይገኛሉ። እነርሱም፦

  • ደጋ - ከፍታቸው ከባሕር ጠለል 2400 ሜትር የሚጀምር እና የሙቀት መጠናቸው ከ 16 ዲግረ ሴ.ግ የማይበልጥ፤
  • ወይናደጋ - ከፍታቸው ከባሐር ጠለል ከ1500 እስከ 2400 ሜትር፣ ሙቀታቸውም ከ16 ዲግረ ሴ.ግ እስከ 30 ዲግረ ሴ.ግ የሚደርስ፣ እና
  • ቆላ - ከባህር ጠለል በታች ጀምሮ እስከ 1500 ሜትር ከፍታ ያላቸው፣ የሙቀት መጠናቸውም ከ30 ዲግረ ሴ.ግ እስከ 50 ዲግረ ሴ.ግ የሚደርስ አከባቢዎች ናቸው።

ዋናው የዝናብ ወቅት ከሠኔ አጋማሽ እስከ መስከረም አጋማሽ ሲሆን፣ ከርሱ ቀደም ብሎ አልፎ አልፎ የሚጥል የበልግ ዝናብ በየካቲት እና በመጋቢት ይከሰታል። የተቀሩት ወራት በአብዛኛው ደረቅ ናቸው።

አስተዳደራዊ ክልሎች

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጽያ ውስጥ 9 አስተዳደራዊ ክልሎች ይገኛሉ። አወቃቀራቸውም በህገመንግስቱ በተደነገገው መሰረት «በህዝብ አሰፋፈር፤ ቋንቋ፤ ማንነት እና ፈቃድ ላይ» ተመስርቶ ሲሆን ክልሎቹም ፦

ሕዝብ

ኢትዮጵያ ከ80 በላይ የሚሆኑ ብሄረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የምተችል ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች የኦሮሞ፣ የአማራ፣ እና የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የአገሪቱዋ ሕዝብ ቁጥር ክ3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች እስልምና እና ክርስትና በስፋት የሚተዋልባት አገር ናት። እስልምና ከ 40-45% ፡ ክርስትና ከ 35-40% እንዲሁም ሌሎች ከ 10-20% እንደሆነ ጥናቶች ይጠቁማሉ።

ቋንቋዎች

በኢትዮጵያ ውስጥ ከ80 በላይ ብሄር ብሄረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ80 በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት፡፡ በአሁኑ ወቅት በእብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የብሄራዊ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ የሚነገሩት ቋንቋዎች ወደ አራት ዋና ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላል። እነዚሁም

ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ ኦሮምኛሶማልኛአፋርኛሲዳምኛሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛኩናማኛጉሙዝኛሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። እንደ ወላይትኛጋሞኛከፋኛሃመርኛ የመሳሰሉት የኦሞአዊ ቋንቋ ዘሮች ሲሆኑ አማርኛ፣ ትግርኛጉራጊኛስልጢኛሀደሪኛ እና መሰል ቋንቋዎች ከሴማዊ ቋነቋዎች ይመደባሉ።
የሴሚቲክ ምንጭ ያላቸው እንደ አማርኛ ያሉት ቋንቋዎች የራሱ የሆነ የተለየ የፊደል ስርአት ያላቸው ሲሆን ይህም ኢትዮጵያን ከአፍሪቃ ብቸኛዋ ባለ ጥንት ፊደል ሀገር ያደርጋታል። እነኚህ የሴሚቲክ ምንጭ ያላችው ቋንቋዎች ግዕዝ የተባለ በአሁኑ ወቅት ከቤተክርስትያን ውጭ ለእለት ተእለት ግልጋሎት ላይ የማይውል ግንድ ዘር አላቸው።

ምጣኔ-ሃብት

ባህል እና ሃይማኖት

የህዝብ በዓላት (የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የሚለውንም ተመልከት)
ቀን የበዓሉ ስም የበዓሉ ስም በእንግሊዝኛ አስተያየት
መስከረም ፩ እንቁጣጣሽ Ethiopian New Year  
መስከረም ፲፯ መስቀል Finding of the True Cross  
ጥቅምት ፳፬ ኢድ አል ፈጥር End of Ramadan ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም. ነው
ታህሳስ ፳፱ ገና Christmas  
ጥር ፪ ኢድ አል አደሃ Eid ul-Adha (Feast of the Sacrifice) ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም.ነው
ጥር ፲፩ ጥምቀት Epiphany  
የካቲት ፳፫ የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል Battle of Adowa Commemoration Day  
ሚያዚያ ፬ መውሊድ (የነብዩ መሃመድ የልደት ቀን) Birthday of The Prophet Muhammad ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም. ነው
ሚያዚያ ፲፫ ስቅለት Good Friday (Crucifixion) ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም. ነው
ሚያዚያ ፲፭ ትንሳዔ (ፋሲካ) Easter ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ1998 ዓ.ም. ነው
ሚያዚያ ፳፯ የጀግኖች አርበኞች መታሰቢያ ቀን Patriots' Day  
ግንቦት ፳ ደርግ የወደቀበት ቀን End of the Derg Regime  
በ"Wikimedia Commons"
(የጋራ ፎቶዎች ምንጭ)
ስለ ኢትዮጵያ የሚገኛኙ
ተጨማሪ ፋይሎች አሉ።


ኢትዮጵያ

ታሪካዊ ቦታዎች - አክሱም | ላሊበላ | ጎንደር | ነጋሽ | ሐረር | ደብረ-ዳሞ | አዲስ አበባ
አስተዳደራዊ ክልሎች - ትግራይ | አፋር | አማራ | ኦሮሚያ | ሶማሌ | ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል | ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች | ጋምቤላ | ሐረሪ | አዲስ አበባ | ድሬዳዋ
ቋንቋዎች - አማርኛ | ግዕዝ | ኦሮምኛ | ትግርኛ | ጉራጊኛ | ሶማሊኛ | አፋርኛ | ሲዳምኛ | ሃዲያኛ | ከምባትኛ | ወላይትኛ | ጋሞኛ | ከፋኛ | ሃመርኛ | ስልጢኛ | ሀደሪኛ
መልክዓ-ምድር - አባይ | አዋሽ | ራስ-ዳሽን | ሶፍ-ዑመር | ጣና | ደንከል | ላንጋኖ | አቢያታ | ሻላ
ከተሞች - የኢትዮጵያ ከተሞች