መስኪአጝ-ኑና

ከውክፔዲያ

መስኪአጝ-ኑናሱመራዊ ነገሥታት ዝርዝር ዘንድ በሱመርኡር ከተማ ላይ የንጉሥ መስ-አኔ-ፓዳ ልጅና ተከታይ ነበረ። 36 አመት ሙሉ እንደ ነገሠ ሲል ይህ ግን ታማኝ መረጃ አይደለም። ከሥነ ቅርስ ኅልውነቱ ተረጋገጠ፣ ስሙ በአንድ አካድኛ ጽሑፍ በንግሥቱ እቃ ላይ በኡር ተገኝቷል። የቱማል ጽሑፍ በሚባለውም መዝገብ መሠረት መስኪአጝ-ኑና ከአባቱ መስ-አኔ-ፓዳ ቀጥሎ የኒፑር መቅደስ ጠባቂ ነበረ።

በዝርዝሩ ዘንድ ከመስኪአጝ-ኑና በኋላ ኤሉሉ እና ባሉሉ በኡር ነገሡ፣ ከዚያ ኤላማዊው የአዋን ሥርወ መንግሥት ተነሥቶ ሱመርን ለጊዜው ያዘ። ኤሉሉ በኤሪዱ ግንብ ላይ ሥራውን እንዳስቀጠለው የሚል አንድ ቅርስ ብቻ አለ። ስለ ባሉሉም አንዳችም ቅርስ ወይም ጥቅስ አልተገኘምና ኤሉሉና ባሉሉ በመላ ሱመር ላዕላይነቱን እንደ ያዙ አጠያያቂ ነው። ስለዚህ ኤላም የገባው በመስኪአጝ-ኑና ዘመን መጨረሻ (ምናልባት 2310 ዓክልበ. ግድም) እንደ ነበር ይመስላል፤ ኤሉሉ እና ባሉሉም ምናልባት የኡር ከተማ ገዢዎች ብቻ ሊሆኑ ይቻላል።

ቀዳሚው
መስ-አኔ-ፓዳ
ሱመር (ኒፑር) አለቃ
2314-2310 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
የአዋን ንጉሥ
ዑር ንጉሥ
2314-2262 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
ኤሉሉ