አቫሪስ

ከውክፔዲያ

አቫሪስ (ግሪክኛ፦ Αυαρις /አዋሪስ/፣ ግብጽኛ፦ ሑት-ዋረት፣ ሐዋረት) ጥንታዊ የግብጽ ከተማ ነበረ።

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ «ጣኔዎስ» ወይም «ጣይናስ» በአብርሃም ዘመን ከኬብሮን 7 ዓመታት በኋላ መሠራቱን ሲያመለከት (ኩፋሌ 11:23፣ ኦሪት ዘኊልቊ 13፡22)፣ የዚሁ አቫሪስ ሥፍራ ማለት ሳይሆን አይቀርም። በሂክሶስ ዘመን የሂክሶስ ዋና ከተማ ሆነ። በኋላ (1548 ዓክልበ. ግድም) የግብጽ ኗሪ 18ኛው ሥርወ መንግሥት ፈርዖን 1 አህሞስ አቫሪስን ይዞ የሂክሶስ ወገን ከግብጽ አውጥቶ ወደ እስያ (ከነዓን) እንደ መለሳቸው ይመስላል። በ19ኛው ሥርወ መንግሥት በአቫሪስ አጠገብ አዲስ ዋና ከተማ ፒ-ራምሴስ ተሠራ።

ከአቫሪስ ቤተ መንግሥት ፍርስራሽ የተገኘው የግድግዳ ስዕል በክኖሦስ (ቀርጤስ) ፈሊጥ ነው።