ዊቴሊዩስ

ከውክፔዲያ
ዊቴሊዩስ የሮሜ ቄሣር

አውሉስ ዊቴሊዩስ ለአጭር ዘመን ለ፰ ወር ከሚያዝያ ወር 61 ዓም ጀምሮ የሮሜ መንግሥት ቄሣር ነበር። የአራቱ ቄሣሮች ዓመት ሦስተኛው ንጉሥ ነበረ።

ዊቴሊዩስ በ7 ዓም በጣልያን ተወለደ። በካፕሪ ደሴት ግቢ፣ ነጉሥ ቲቤርያስ እንደ ጎበዝ ልጅ ቆጠረው፣ እንዲሁም ለሰዶማውያን ነገሥታት ካሊጎላኔሮን ተወዳጅ ነበረ።

ኔሮን ዓርፎ ጋልባ ቄሣር እንደ ሆነ፣ ዊቴሊዩስ የጌርማኒያ አገረ ገዥ አድርጎ ሾመው። በጌርማኒያ ግን ሥራዊት በጋልባ ላይ አመጸና ዊቴሊዩስ ቄሳር ተብሎ አወጁት።

የዊቴሊዩስ መሀለቅ

ጋሊያ (ፈረንሳይ)፣ ብሪታኒያራይቲያ (ስዊስ) ክፍላገራት ሥራዊት ደግሞ ዊቴሊዩስን ደገፉ። ስራዊቶቹ በጣልያን ደርሰው ግን በጋልባ ፈንታ ኦጦ ቄሣር ሆኖ አገኙት። ኦጦ በቀላል ተሸነፈና ዊቴሊዩስ ቄሣር ሆነ። በይፋ «ቄሣር» በሚለው ማዕረግ ፈንታ አዲስ ማዕረግ «ጌርማኒኩስ» ተባለ። እንደ ቅድመኞቹ ጨካኝና መረን ፈላጭ ቁራጭ ነበር፣ ብዙ ሰዎች ለደስታው ገደለ። በተጨማሪ የታሪክ ጸሐፊዎች እንደሚሉ እጅግ ሆዳም ሰው ነበር፣ አራት ጊዜ በየቀኑ ታላቅ ግብዣ በቅንጦት ይበላ ነበር።

ከጥቂት ወራት በኋላ በሐምሌ 61 ዓም፣ የምሥራቅ ክፍላገሮች ስራዊቶች አለቆቻቸውን ቤስጳስያን እንደ ቄሣር በአመጽ ሾሙት። ይህ የሞይስያፓኖኒያሶርያ እና ይሁዳ ክፍላገራት ሥራዊት ለቤስጳስያን የደገፉት ነው። በታህሳስ ወር 62 ዓም. የቤስጳስያን ወገን ሲያሸንፍ ዊቴሊዩስ ራሱን ለመደብቅ ሲሞክር፣ በቤስጳስያን ሥራዊት ተገኝቶ ተገደለ። ቤስጳስያንም ያንጊዜ ቄሣር ሆኑ።