የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት

ከውክፔዲያ

የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት' የሚለው የኢትዮጵያ "ሕገ ሕዝብ" ተብሎ ቢጠራ መንግስት እሚለውን በሕዝብ በመተካት አመሰራረቱ አሁን ባለው ተኮርጆ የተጻፈ ከምእራባውያን የተቀዳ በተግባር የማይፈጸም በመሆኑ፡ ለወደፊቱ የሀገሪቱ መመርያ ከሕዝቡ የወጣ ከያንዳንዱ ግዛት ከምክትል ወረዳ ጀምሮ እስከ ክፍለ ሀገር፡ ያለባቸውን ችግርና መፍትሔ የሚመሩበት ሕግ በማውጣት፡ ባጠቃላይ ሁሉንም ጎሳዎች ሊያስተናግድ የሚችል ሕግ በመቅረጽ፡ በሁሉም ሕዝቦች ድምጽ የጸደቀ፡ የማይሻር ከስልጣን የሚቀመጡት የማይቀየር የማሻሻያና፡ በሕዝብ ሸንጎ የሚፈጸም እንዲሆን ቢደረግ አስፈላጊ ብዮ አምንበታለሁኝ። የኢትዮጵያ ህገ መንግስት አማራ ጠል እና ህዝቦችን በቋንቋ ከፍሎ ደም የሚያቅባ የእልቂት ሰነድ ከመሆኑ በላይ ህዝቦች የስነ ልቦና ውቅር አፍርሶ በዝረኝነት ያውቅረና የሃገርን ህልውና አድጋ ላይ የጣለ ሰነድ ነው።

ምክንያቱም ሕግ የሁሉም በላይ ሆኖ ሁሉንም እንዲያስተናግድ ተፈጻሚነትም እንዲያገኝ የሕግ አውጮችና መሪና ተመሪዎችን ቤኩል ማስተናገድ ሁሉም ተገዥዎች መሆን ገባቸዋል፡ የሰው ልጅ መብት በፍጹም መደፈርና በሕግ ስም መደርመስ አይገባውም ይህ ከተፈጥሮ የተሰጠው በመሆኑ መጠበቅ ይኖርበታል። ሰብዓዊ መብት ማንኛውም ዜጋ መብቱና ነፃነቱን የማይነጠቅ አሳልፎም የማይሰጥ በመሆንኑ፡ በማንኛውም መንገድ በሰውነቱ በሕይወቱ ጉዳት ቁስልና ጠባሳ የሚያደርስ ጥሰት እንዳይገኘው፡ በስልጣን ያለው የስራዓቱ አገልጋዮች እንዳይደርስበት ደሕንነቱ ነፃነትና መብቱ መጠበቅ ግዴታ አለባቸው።

ለዚህም ሁሉም ዜጎች ግዴታቸውን ለመፈጸምና መብታቸውን ለማስጠበቅ በዚህ ጉዳይ በመግባት ይጠቅማል ብለን የምናስበውን የየበኩላችን አስተዋጻኦ በማድረግ በሀገራችን እያንዣበበ ያለውን የማፍረስ የሕዝቦች መነጣተል ጉዳይ ለመታደግ ያስችላል። ሰላማችን ያብዛው

ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

1) የ1931 የሀይለስላሴ ህገ-መንግስት

-የመጀመሪያ የኢትዮጵያ ዘመናዊ ህገ-መንግስት ነው፡፡

-ፍትሀ ነገስትን ለመተካት የመጣ ህገ-መንግስት ነው፡፡

-ህገ-መንግስቱ መምጣቱ ለመጀመሪያ የታወጀው በሀይለስላሴ ጊዜ በሀምሌ 16 1931 ዓ.ም የተካሄደ ታላቅ ድግስ ላይ ነው፡፡

-7 ምዕራፍና 55 ንዑስ ምዕራፍ አሉት፡፡

1ኛ ምዕራፍ- ስለ ስልጣን ርክክብ ሁኔታዎች ስለ አልጋ ወራሾች

2ኛ ምዕራፍ- የሀይለስላሴ ስልጣን

3ኛ ምዕራፍ- ስለግዴታዎች እና በሀይለስላሴ እውቅና ስለተሰጣቸው መብቶች

4ኛ ምዕራፍ- ስለ ኢትዮጵያ ፓርላማ

5ኛ ምዕራፍ- ስለ ሚኒስቴሮች

7ኛ ምዕራፍ- ስራ በጀት አወጣጥ

-ይህ ሕገ-መንግስት ለ26 አመታት አገልግሏል፡፡

2) የ1955 የሀይለስላሴ ህገ-መንግስት

-እ.ኤ.አ በህዳር 1955 አፄ ሀይለስላሴ አዲስ የተሻሻለ ህገ-መንግስት አወጀ፡፡

-የ1931 ህገ-መንግስት የተሻሻለበት ምክንያት፦

1ኛ ከአለም አቀፍ ማህበረሰብ ጋር ያለውን ግንኙነት ለማሻሻል

2ኛ ኤርትራን በተመለከተ አዲስ ህግ በማስፈለጉ ምክንያት ነው

-ህገ-መንግሰቱ 8 ምዕራፍና 131 ንዑስ ምዕራፎች አሉት፡፡

-ይህ ህገ-መንግስት በ1974 ደርግ ሲገባ ተሽሯል፡፡

-በ1974 የሀይለስላሴ መንግስት ከተሻረ እና ደርግ ከገባ በኃላ ደርግ ለ11 ዓመት ያህል ያለ ህገ-መንግስት በስልጣን ላይ ነበር፡፡

-ከዚያ በኃላ የወጣው የደርግ ህገ-መንግስት ለአራት አመታት ያህል አገልግሏል፡፡

3) የ1987 ህገ-መንግስት

-ይህ የኢትዮጵያ ሶስተኛ ህገመንግስት ነው፡፡

-ጥቅም ላይ መዋል የጀመረው የካቲት 22 1987 ዓ.ም ሲሆን የተፃፋው በየካቲት 1 በተደረገ ህዝበ-ውሳኔ የተነሳ ነው፡፡

-የሰራተኛ ፓርቲ በ1984 ከተመሰረተ በኃላ አንደኛ ቀዳሚ ስራ ተግባሩ አዲሱን ብሔራዊ እና የኢትዮጵያን ህዝባዊ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሊመራ የሚችል ህገ-መንግስት መመስረት ነበር፡፡

-የ1987 ህገ-መንግስት 17 ምዕራፍ እና 119 ንዑስ ምዕራፎች ነበሩት 4) የ1995 ህገ-መንግስት

-ኢትዮጵያ በአሁን ጊዜ እየተገለገለባቸው ያለው ህገ-መንግስት ነው፡፡

-ይህ ህገ-መንግስት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የበላይ ህገ-መንግስት ነው፡፡

-ህገ-መንግስት የተራቀቀው በ1994 በተመረጠው አርቃቂ ኮሚቴ ነው፡፡

-በስራ ላይ የዋለው በኢትዮጵያ የሽግግር መንግስት በታህሳስ 1994 ነው፡፡

-የፀደቀው ከግንቦት-ሰኔ 1995 ባለው ጊዜ በተካሄደው ከአጠቃለይ የመንግስት ምርጫ ተከትሎ ነው፡፡

-ህገ-መንግስቱ 11 ምዕራፍና 106 አንቀፆች አሉት፡፡

ጥንታዊ የኢትዮጵያ ህገ መንግስት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ጥንታዊው የኢትዮጵያ ህገ መንግስት በማን ተመሠረተ? አመተ ምህረቱስ? እንደሚታወቀው ከሆነ 4 የመጀመሪያ ህገ መንግስቶች አሉ። የመጀመሪያው ህገ መንግስት የወጣው በሀይለ ስላሴ ዘመነ መንግስት ሲሆን ዓ.ምቱ ደግሞ

ዘመናዊ ሕገ መንግስት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ፲፱፻፳፫ ዓመተ ምኅረት በቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ ፲፱፻፵፰ ዓ.ም. ካገለገለ በኋላ በዚያ ዓመት የንጉሠ ነገሥቱ ኢዮቤልዩ የዘውድ በዓል በሚከበረበት ዕለት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት አብዮት እስከፈነዳበት ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. ድረስ በአገልግሎት ላይ ከዋለ በኋላ በደርግ ውሳኔ፣ ሕገ መንግሥታዊ ባልሆነ ሂደት ተሰረዘ።