የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን

ከውክፔዲያ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ኃይማኖት ተከታዮች በተለይም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ በ፴ ዓ/ም በፈለገ ዮርዳኖስ በመጥምቁ ዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ባሕር የተጠመቀበትን ዕለት የሚያስታውሰው፣ ኤጲፋንያ በመባልም የሚታወቀው ደማቅ በዓል ነው። መገለጥ፣ መታየት ማለት ነው። የኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት ታሪክ የሚገኘው በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፫ ቁ ፲፫–፲፯ ውስጥ ነው። ጌታ

በአገራችን፣ ጥር ፲ ቀን፣ በከተራ፣ በገጠር ወራጅ ውሃ የሚከተርበት፣ ታቦታት ከየአቢያተ ክርስቲያናቱ በዓሉ ወደሚከበርበት ቦታ በምዕመናን ታጅበው በዝማሬና በሆታ ይሄዳሉ። እዚያም በተዘጋጀ አቡነ ባስልዮስእስክንድርያ ፓትርያርክ አቡነ ዮሳብ 2ኛ የጵጵስና ማዕረግ ተቀበሉ። ኢትዮጵያም፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እራሷን የቻለች ሆነች። ወደ ፶፭-፷ ሚሊዮን የሚቀርቡ ምእመናን ሲኖሩት ከምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ትልቁ ነው።

በታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

መሠረቶች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

«ተዋሕዶ» ከልሣነ ግእዝ የመነጨ ቃል ሲሆን፣ ትርጒሙም "አንድ ሆኖ" ማለት ነው። ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ በተዋሕዶ ከበረ ማለት ነው። ለዚሁም በዐረብኛ ተመሳሳይ ቃል "ታውሒድ" ሲባል፣ በአንድ አምላክ ብቻ ማመን የሚለውን ፅንሰ ኣሳብ ያመለክታል። በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ቃሉ የሚነካ የክርስቶስ ባሕርይ በ"ሰብዓዊ" እና በ"መለኮታዊ" ተለይቶ ሳይሆን አንድ ብቻ እንደሆነ የሚለው ጽኑ እምነት ነው።

443 ዓ.ም. (451 እ.ኤ.አ.) በሮማው ንጉሥ መርቅያን ዘመነ መንግሥት ፮፻፶ ኤጲስ ቆጶሳት በተገኙበት የተሰበሰበው የኬልቄዶን ጉባኤ ከሮማው ሊቀ ጳጳሳት ቀዳማዊ ልዮን "ክርስቶስ ሁለት የተለያዩ ባሕርያት አሉት" የሚል ጽሑፍ አቅርቦላቸው ነበር። ዳሩ ግን የእስክንድርያው ፓትርያርክ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ "ጌታ ሁለት ባሕርያት አሉት" የሚለው ትምሕርት ስሕተት ነው ብሎ ልዮንን አወገዘው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት በእምነት ተለያዩ። የቅዱስ ዲዮስቆሮስን ትምሕርት የሚከተሉ ዛሬ የአርሜኒያ፣ የሕንደኬ፣ የግብፅ፣ የሶርያ፤ የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ናቸው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት ጌታችን መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ከሁለት አካል አንድ አካል በመንሳት ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ ማለት ነው።

የቤተ ክርስቲያን መመስረት በኢትዮጵያ የተጀመረው በወንጌል ሰባኪ ቅዱስ ፊልጶስ መሆኑ ይታወሳል (ሐዋርያት ምዕራፍ ፰)፦

«እነሆም፥ ህንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘቧም ሁሉ የሰለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር...»

በዚህ ንባብ ዘንድ ፊልጶስ ጃንደረባውን የትንቢተ ኢሳይያስ ክፍል እንዲገባው አስረድቶት በክርስትና አጠመቀው። ንግሥት ግርማዊት ህንደኬ ፯ኛ ከ፴፬ ዓ.ም. እስከ ፵፬ ዓ.ም. ገደማ በኢትዮጵያ የነገሡ ናቸው።

በ፬ኛው ምዕት ዘመን በወንድማማቾቹ በንጉሥ ኤዛና እና በንጉሥ ሳይዛና ዘመን በፍሬምናጦስ አማካይነት ክርስትና የግዛቱ ይፋዊ ሃይማኖት ሆነ። ይህ ፍሬምናጦስ በኢትዮጵያ «አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን» ተብሎ ይታወቃል። በወጣትነት ዕድሜው ከአጎቱ ከፈላስፋው ከመሮፔዎስ እና ከወንድሙ ከሲድራኮስ ጋራ መርከባቸው ስለሰመጠች ከወንድሙ ጋር ከሞት ተርፈው ምጽዋ አጠገብ ተገኙ። ወደ ነገሥታቱም ግቢ አመጧቸውና ቀስ በቀስ ከፍተኛ ተጽእኖ ያለበትን ደረጃን አገኙ። ንጉሥ ኤዛናን ደግሞ ወደ ክርስትና ለውጠው እንዲጠመቁ አደረጉ። ኤዛና ፍሬምናጦስን ለኢትዮጵያ አቡን እንዲሾም ለመጠየቅ ወደ እስክንድርያ ላኳቸውና የእስክንድርያ ጳጳስ አትናቴዎስ ፍሬምናጦስን ሾሞ ላከው። ፍሬምናጦስ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ሲሆን የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ አቡነ ባስልዮስ ደግሞ ፻፲፩ኛው መሆናቸው ነው።

መካከለኛ ዘመን[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

እስላሞች ወደ ግብጽ ከገቡ በኋላ ከእስክንድርያ ጋር የነበረው ግንኙነት ቀጥሏል። ጸሐፊው አቡ ሳሊኅ በ፲፪ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደ ገለጸው፣ ፓትርያርኩ በየዓመቱ ፪ ደብዳቤዎች ለኢትዮጵያና ለኖቢያ ነገሥታት ይጽፉ ነበር። ይህንን አደራረግ ግን አቡ ሃኪም አስቀረ። ፷፯ኛው ፓትርያርክ ቂርሎስ እንደ ኤጲስ ቆሞስ የላኩት ሰቨሩስ ሲሆኑ የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት ሁሉ እንዲያስጠበቁ ታዘዙ። በ፲፬፻፴፩ ዓ.ም. በዓጼ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን አባ ጊዮርጊስ ከአንድ ፈረንሳዊ ጐብኚ ጋራ ስለ ሃይማኖት ስለተነጋገሩ አንድ ተልዕኮ ወደ ሮማ ተላከ።

፲፭፻ ዓ.ም. ደግሞ ኢትዮጵያ ከአዳል ጋር ስትታገል ማቴዎስ የተባለ አንድ አርሜናዊ ወደ ፖርቱጋል ተልኮ የፖርቱጋል ንጉሥ እርዳታን ለመነ። ስለዚህ በ፲፭፻፲፪ ዓ.ም. የፖርቱጋል ሚሲዮን በኢትዮጵያ ደረሰ። በሚከተለው ክፍለ ዘመን ከፖርቱጋል ኢየሱሳውያን የተባሉ ሚሲዮኖች ቤተ መንግሥቱን ወደ ሮማ ካቶሊክ ሃይማኖት ለማዞር ብዙ ጣሩ። በመጨረሻ በ፲፮፻፲፯ ዓ.ም. ንጉሥ ሱስንዮስ ወደ ሮማ ካቶሊክ እምነት ተቀየሩ። ዳሩ ግን የሮማ ሃይማኖት በተዋሕዶ ፈንታ ይፋዊ መሆኑን ሕዝቡ በጣም አልወደደምና በ፲፮፻፳፭ ዓ.ም ሱስንዮስ ዘውዳቸውን ለልጃቸው ለፋሲለደስ እንዲሰጡ ተደረጉ። ፋሲለደስ ወዲያው አገሩን ወደ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መለሱ። ከዚህ በላይ በ፲፮፻፳፮ ዓ.ም ፋሲለደስ ኢየሱሳውያን አገሩን ለቅቀው እንዲሄዱ አዘዙ። በ፲፮፻፶፰ ዓ.ም. መፃሕፍታቸውም እንዲቃጠሉ አዘዙ።

ከሌሎቹ የምትለይበት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የምትቀበላቸው ቅዱሳን መጻሕፍት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኢትዮጵያ ብሉይ ኪዳንን እና ሐዲስ ኪዳንን በሙሉ (ከነዲዩትሮካኖኒካል መፃሕፍት ጋር) በመቀበል ብቸኛ ሃገር ናት። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምትቀበላቸው ቅዱሳት መፃሕፍት ቁጥራቸው ፹፩ ሲሆን እነዚህም ፴፭ የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትና ፵፮ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ናቸው። ይህ የቅዱሳት መጻሕፍት ቁጥር በቀኖና በ፫፻፲፰ቱ አበው ሊቃውንት የኒቂያ ገባኤ ተደንግጓል።

ልሳነ ቅዳሴና ልሳነ ስብከት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ሥነ ሕንፃ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ቤተ ጊዮርጊስ፣ ላሊበላ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሥነ ሕንፃ የቤተክርስቲያናት ትውፊታዊ የሥነ ሕንጻ ጥበቧ አምስት ዓይነት ነው። እነርሱም ክብ፥ መስቀል ቅርፅ፥ ዋሻ፥ ፍልፍል እና ስቀልማ ናቸው። ክብ ሕንጻ አብያተ ክርስቲያናት በብዛት በገጠሪቷ ኢትዮጵያ የሚገኙ ሲሆን፣ መስቀል ቅርጽ ያላቸው ደግሞ በከተማ አካባቢ ይገኛሉ። ዋሻ አብያተ ክርስቲያናት በብዛት በተራራማ አካባቢዎች ሲገኙ፣ ፍልፍል አብያተክርስቲያናት ደግሞ ከአንድ ቋጥኝ ተፈልፍለው የተዘጋጁ ናቸው። ሰቀልማ የሚባለው እንደ ጎንደሩ ደብረ ብርሃን ሥላሴ ያሉ አብያተ ክርስቲያናት ናቸው።

ታቦት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ትምህርት ሃይማኖት (የሃይማኖት ትምህርት) በሁለት ይከፈላል። ይኸውም፦ 1ኛ) ዶግማ፣ 2ኛ) ቀኖና በሚል ነው። 'ዶግማ' ቃሉ የግሪክ ሲሆን ፍችውም እምነት ማለት ነው።

'ቀኖና' ደግሞ ቃሉ የግሪክ ሲሆን ሥርዓት ማለት ነው። ከእነዚህ ከሁለቱ ዶግማ ወይም እምነት አይጨመርበትም፤ አይቀነስበትም፤ አይሻሻልም፤ ችግርና ፈተናም ቢመጣ እስከ ሞት ድረስ አጥብቀን የምንይዘው ነው። ለምሳሌ ያህል፣ ይህን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ የፈጠረ፤ ቢመረምር እንጂ የማይመረመር ሁሉን ቻይ አምላክ፤ የሚሳነው ነገር የሌለ ፈጣሪ፤ የሰማይና የምድር ባለቤት፣ የሠራዊት ጌታ ሕያው እግዚአብሔር ነው።

እግዚአብሔር (ፈጣሪ) የአካል ሦስትነት አለው። በመለኮት፣ በመፍጠር፣ በሥልጣን፣ በአገዛዝ፣ በፈቃድ እና በመሳሰሉት ግን አንድ ነው። በሦስትነቱ አብ፥ ወልድ፥ መንፈስ ቅዱስ ሲባል፣ በአንድነቱ አንድ መለኮት፥ አንድ እግዚአብሔር ይባላል። በአዳም ምክንያት ከመጣው የዘለዓለም ሞትና ከዲያብሎስ ባርነት ነፃ የወጣነው ከሦስቱ አካላት በአንደኛው አካል ማለትም በወልድ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ይህ ዶግማ ወይም እምነት ይባላል።

ቀኖና ግን በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ያደጉ ክርስቲያኖች የሚመሩበት ሥርዓት ስለሆነ፣ በሃይማኖት አባቶች ወይም በቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት እንደጊዜው ሁኔታ የሚሻሻል በመሆኑ የሚጨመርበት፣ የሚቀነስለት ነው። ለምሳሌ ያህል እኛ ኦርቶዶክሳውያን የምንጠመቀው ሴት በተወለደች በሰማንያ ቀን፣ ወንድ በተወለደ በአርባ ቀን ነው። የተወለዱ ሕፃናት፣ ሴቷ ሰማንያ ወንዱም አርባ ቀን ሳይሞላቸው ቢታመሙና በሽታው አስጊ ቢሆን የግድ የተባለው ቀን ሳይጠበቅ በ10፣ በ20፣ በ30…ቀናቸው መጠመቅ ይችላሉ ቀኖና ነውና። በቤተ ክርስቲያናችን የቀዳስያን ብዛት መነሻው አምስት ነው። ምናልባት ከአምስቱ አንዱ፣ ሁለቱ፣ ሦስቱ ቢታጡና ሌላም ተፈልጎ እስከ መጨረሻ የማይገኝ ከሆነ፣ ከአቅም በላይም የሆነ ችግር ከገጠመ፣ ሁለቱ ወይም አንዱ ብቻ ቀድሰው ማቁረብ ይችላሉ፤ ቀኖና ነውና። በቤተ ክርስቲያናችን ታቦት ሲከብር ቤተ ክርስቲያኑን የሚዞረው ሦስት ጊዜ ነው፥ ችግር ካለ አንድ ጊዜ ብቻ ዑደት ተፈጽሞ ሊገባ ይችላል። ቀኖና ነውና፤ ስለቀኖና (ስለሥርዓት) ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ እንዲህ ሲል ጽፏል።

1. "ነገር ግን ሁሉን በአግባብና በሥርዓት አድርጉ" 1ኛ ቆሮ. 14፥40። 2. "ወንድሞች ሆይ በሠራንላቸው ሥርዓት ሳይሆን በተንኮል ከሚሄዱት ወንድሞችን ሁሉ ትለዩ ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዝዛችኋለን። እኛን ልትመስሉ እንደሚገባችሁ እኛም በእናንተ መካከል ያለ ሥራ እንዳልኖርን ራሳችሁ ታውቃላችሁ" 2ኛተሰ. 3፥6-7። ቀኖና (ሥርዓት) የሚወሰነው በሃይማኖት አባቶች እንደሆነና ወንጌልን የሚያስተምር ሰው ለሚያስተምራቸው ክርስቲያኖች በሃይማኖት አባቶች የተወሰነ ቀኖና ማስተማርና ትምህርት መሰጠት እንዳለበት መፅሐፍ ቅዱስ እንዲህ ሲል ያስረዳል።

"በየከተማውም ሲሄዱ፣ ሐዋርያትና ቀሳውስት በኢየሩሳሌም ያዘዙትን (የወሰኑትን) ሥርዓት አስተማሯቸው። አብያተ ክርስቲያናትም በሃይማኖት ፀኑ፤ ዕለት ዕለትም ቁጥራቸው ይበዛ ነበር" ይላል የሐዋ. 16፥4-5። በዚህ የእግዚአብሔር ቃል መሠረት ቅዱስ ጳውሎስ ደርቤንና ልስጥራን በተባሉ ቦታዎች ለነበሩ ክርስቲያኖች ወንጌልን ከሰበከ በኋላ ሐዋርያት የወሰኑትን ቀኖና (ሥርዓት) እንደሰጣቸው እንረዳለን። ስለዚህ ቀኖና ወይም ሥርዓት ቤተ ክርስቲያንን ይጠቅማል እንጂ አይጎዳም። በመሆኑም ዶግማንና ቀኖናን ወይም እምነትንና ሥርዓትን ጎን ለጎን ይዞ መጓዝ ሐዋርያትን መከተል እንጂ ወደ ኋላ ተመልሶ አይሁድን መከተል አይደለም። እንግዲህ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን የሚቃወሙ ሰዎች ሁሉ፣ የሚቃወሙት በቀኖና (በሥርዓት) የሚመሩትን ክርስቲያኖች ሳይሆን የእግዚአብሔር ቃል የሆነ መፅሐፍ ቅዱስን በመሆኑ እንዳይሳሳቱ አደራ እንላለን።

አሁን እንግዲህ የዶግማንና የቀኖናን ልዩነት ከተረዳን በቀጥታ ወደ ታቦቱ ጥያቄ እንሄዳለን።

ጥያቄ 1፦ ዛሬ በእኛ ቤተ ክርስቲያን ያለው ታቦት ነው? ወይስ በታቦትና በጽላት መካከል ልዩነት አለ?

መልስ፦ ታቦት የጽላት ማደሪያ ነው፤ ዘዳ 40፥20። ጽላት ደግሞ ቅዱስ ቃሉ የተጻፈበት ሰሌዳ ማለት ነው፤ ዘዳ 34፥27-28። ስለዚህ እነዚህ ሁለት ነገሮች ዛሬም በሐዲስ ኪዳን አሉ። ሆኖም ግን አሠራሩ ሙሉ በሙሉ በዘጸ 25፥10-18 ያለውን የሙሴን ሕግ የተከተለ አይደለም። ምክንያቱም፦

1ኛ፦ ታቦት እንደሙሴ ሕግ የሚዘጋጀው ከግራር እንጨት ሆኖ፣ ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፣ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል፣ ቁመቱም አንድ ክንድ ተኩል ይሁን ይልና፣ በውስጥና በውጭም በጥሩ ወርቅ ለብጠው፣ በዙሪያውም የወርቅ አክሊል አድርግለት ይላል። ደግሞም ታቦቱን የሚሸከሙት ከወርቅ በተሠሩ መሎጊያዎች አራት ሰዎች እንደሆኑ እንረዳለን። በአጠቃላይ የብሉይ ኪዳን የታቦት አሠራር እጅግ ከባድ በመሆኑ በሁሉም ዘንድ አይቻልም ነበር። ምናልባት አንዳንድ የቤተ ክርስቲያን ፍቅር የነበራቸው ነገሥታትና ዛሬም ፍቅረ ቤተ ክርስቲያን ያላቸው አንዳንድ ምዕመናን ይችሉት እንደሆነ ነው እንጂ ቀላል ኣይደለም።

2ኛ፦ ጽላት እንደሙሴ ሕግ ከሆነ መዘጋጀትና መጠረብ ያለበት ከከበረ ድንጋይ ነው። በአንድ ታቦት ውስጥም መቀመጥ ያለባቸው ሁለት ጽላቶች ናቸው፤ ዘዳ 34፥1። በአጠቃላይ እንደ ብሉይ ኪዳኑ ሕግና ሥርዓት ከባድ ነው። የብሉይ ኪዳኑ ሥርዓትም ለሐዲስ ኪዳኑ ሥርዓት ጥላ ሆኖ አልፏል፤ 2ኛ ቆሮ 3፥7-11፤ ቆላ 2፥17፤ ዕብ 10፥1።

እንግዲህ እዚህ ላይ የሐዲስ ኪዳኑ ታቦትና ጽላት የብሉይ ኪዳኑን የታቦት አሠራርና ሥርዓት ጠንቅቆና ተከትሎ የማይሄድ ከሆነ፣ "ይህ የብሉይ ኪዳኑን የታቦትና የጽላት አቀራረጽ ሥርዓት ጠንቅቆ ያልሄደ የሐዲስ ኪዳን ታቦትና ጽላት ከየት መጣ?" የሚል ጥያቄም ሳያስነሳ አይቀርም።

አንባብያን ሆይ በቀጥታ ወደ ጥያቄው ከመግባታችን በፊት በዚህ ፅሑፍ ስለዶግማና ቀኖና ማብራሪያ የሰጠነው ይህን ለመሰለው ጥያቄ እንዲጠቅም ነው። አሁን ወደ ሐዲስ ኪዳን ታቦትና ጽላት ስንሄድ ቁም ነገሩ እንደሚከተለው ነው።

የሐዲስ ኪዳን የታቦትና የጽላት አቀራረጽም ሆነ አጠቃቀሙ የተወሰነውና የሚወሰነው በቀኖና ነው። ቀኖና ደግሞ እንደ ሁኔታው የሚሻሻል ነው። ሲቻል ይጨመርበታል፣ ሳይቻል ደግሞ ይቀነስለታል። እንግዲህ በቤተ ክርስቲያናችን ቀኖና ካበረከታቸው ነገሮች አንዱ የሐዲስ ኪዳን የታቦትና የጽላት አቀራረጽንና አጠቃቀምን ነው።

ስለዚህ በሐዲስ ኪዳን ታቦትን ለመቅረጽ የግራር እንጨት ባይገኝ በዘፍ 1፥31 ላይ "እግዚአብሔርም የፈጠረውን (ያደረገውን) ሁሉ እጅግ መልካም እንደሆነ አየ" ስለሚልና፣ እግዚአብሔር የፈጠረውን ስለማይንቅ፣ ከግራር ሌላ ከማይነቅዝ እንጨት መቅረጽ እንችላለን። ቁመቱ፣ ወርዱና ዙሪያውም እንደችሎታችን ይሆናል። በውስጥና በውጭ ስለሚሆነው የወርቅ ክብርም እንደችሎታችን ይወሰናል። ከሌለንም ወርቁ ይቀራል፣ ቀኖና ነውና።

ስለጽላቱም እንደዚሁ ነው፥ ከቻልን ከከበረ ድንጋይ፣ ከዕብነ በረድ መቅረጽ እንችላለን፤ ካልቻልን ጽላቱን ከማይነቅዝ እንጨት መቅረጽ እንችላለን። በሌላ በኩልም ከቻልን እንደ ብሉይ ኪዳኑ በአንድ ታቦት ሁለት ጽላት ማስቀመጥ እንችላለን፤ ካልቻን በአንድ ታቦት አንድ ጽላት ብቻ ይሆናል። በተጨማሪም ጽላቱን ማስቀመጫ ታቦት ባይኖረን፣ ጽላቱን ታቦት ብለን በመጥራት በጽላቱ ብቻ መጠቀም እችላለን፥ ቀኖና ነውና።

በተጨማሪም በኤር 31፥31፤ 2ኛ ቆሮ 3፥1-3፤ በዕብ 8፥8-13፣ የእኛ አካልና ልቡና የርሱ ታቦትና ጽላት ናቸውና "በሐዲስ ኪዳን ለምን ታቦትና ጽላት አስፈለገ? ለምንስ ይህ ሁሉ ተፈጠረ?" የሚሉ አሉ። የክርስቲያኖች አካልና ልቡና በክርስቶስ ደም ታቦት፤ ጽላት፤ ቤተ መቅደስ መሆኑን እናምናለን። ቢሆንም፣ በሐዲስ ኪዳን ታቦትና ጽላት ያስፈለገበት ምክንያት፣ ስለአምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነትና ክብር ሲባል ነው። ምክንያቱም በብሉይ ኪዳን ክብሩን የገለጠበት፣ ቃሉን ያሰማበት፣ ሙሴን እንደባልንጀራ ያነጋገረበት የክብሩ ዙፋን ሆኖ፣ ታቦቱ በውስጡ ለሚቀመጠው ለጽላቱ ማደሪያ በመሆኑ፣ በሐዲስ ኪዳንም የሥጋውና የደሙ የክብር ዙፋን እንዲሆን ሲሆን ስለእኛ በዚህ ዓለም መከራ የተቀበለውን መድኃኔዓለም ክርስቶስን ለማክበር ሲባል ነው።

ጥያቄ 2፦ በዘዳ 31፣18፣ 32፣ 15፣ 134፥1-5፣ 2ኛ ዜና 5፥10 ያሉትን ጥቅሶች በመጥቀስ እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠው ሁለት ጽላቶችን ብቻ ነው። ነገር ግን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እነዚህን እልፍ አእላፋት ጽላት ከየት አመጣቻቸው? አራብታችሁ ቅረጹ የሚል አለ ወይ?

መልስ፦ በዘዳ 32፥19 ስንመለከት እግዚአብሔር ራሱ አዘጋጅቶ ለሙሴ የሰጠውን ሁለቱን ጽላት እሥራኤል ጣዖት ሲያመልኩ ስላገኛቸው ሙሴ ተበሳጭቶ ሰብሯቸዋል። ነገር ግን ቸርነቱ ለዘለዓለም የሆነ እግዚአብሔር አምላክ ለሙሴ የመጀመሪያዎቹን አስመስሎ እንዲሠራ ነገረው፤ ሙሴም አስመስሎ ሠራ። በዘዳ 34፥1-5 መሥራት ብቻ ሳይሆን ኣሥሩን የቃል ኪዳን ቃላትም በጽላቱ ላይ እንዲፅፍ ሙሉ ሥልጣን ከእግዚአብሔር ተሰጠው። ሙሴም ተፈቅዶለታልና አሥሩን ቃላት በጽላቱ ላይ ጻፈ። ዘዳ 34፥27-28 ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ጽላትንም ሆነ ታቦትን እያስመሰሉ ለመሥራት ሙሉ ሥልጣንን አግኝተናል። ይህን በተመለከተ አንዳንድ አባቶች፦ "አዳም እንኳን በደለ አዳም ባይበድል ኖሮ አምላክ ሰው ሆኖ በቀራንዮ ስለእኛ የመሰቀሉን፣ ስለኛ የመሞቱን የፍቅር ምስጢር አናውቀውም ነበር" ይላሉ። "እስራኤልም በጥጃ ምስል ጣዖት አምልከው እንኳን በደሉ፣ እሥራኤል ባይበድሉ፣ ሙሴ በእግዚአብሔር የተዘጋጁት ሁለቱ ጽላት፣ የሰው ልጅም እግዚአብሔር የሠራቸውን የፊተኞቹን አስመስሎ ለመሥራት ስልጣን ባልኖረውም ነበር፥ ቢሠራም ለምን ሠራህ ለሚለው መረጃ ባላቀረበም ነበር" ይላሉ። ያም ሆነ ይህ ጽላትን አስመስለን፣ አባዝተን፣ አራብተን ለመሥራት መሠረታችን፣ ሥልጣኑ ለኛ ለልጆቹ የተላለፈልን ከአባታችን ከሙሴ ነው።

"ሙሴ የተሰበሩትን አስመስለህ ሁለት ጽላት ቅረጽ ከሚል በቀር ጽላትን አብዝታችሁ፣ አራብታችሁ ተጠቀሙ የሚል ቀጥተኛ ቃል አምጡ" ለሚለው ግን ነገሩ እንዲህ ነው። በብሉይ ኪዳን የጽላትም ሆነ የቤተ መቅደስ ሥርዓት፣ የመስዋዕቱ፣ የዕጣኑ አገልግሎት፣ በኢየሩሳሌም ብቻ ስለነበረና፣ የሌላውም አገር ሕዝብ የሚከተለው የጣዖትን ሥርዓት እንጂ የሙሴን ሥርዓት ባለመሆኑ፣ ጽላቱ ተባዝቶ፣ ተራብቶ ለሌላው አገር ሕዝብ አልተሰጠም። እግዚአብሔርም ከኢየሩሳሌም ውጭ አልፈቀደም፥ የተቀደሰውን ጣዖታውያኑ አሕዛብ ያረክሱታልና። ስለዚህ ስግደቱም፣ የቤተመቅደስ ሥርዓቱም በኢየሩሰሳሌም ብቻ ነበር፤ ዮሐ 4፥18-24።

በኢየሩሳሌም ይኖሩ የነበሩ አሕዛብም "ሰሎሞን ያሠራው ታላቁ ቤተ መቅደስና ሁለቱ ጽላት አንሰውናል፤ በርቀት የምንገኝ እኛ የመንገድ ድካም በዝቶብናል፥ ስለዚህ በያለንበት ቤተ መቅደስ ሠርተን፣ ጽላቱን አክብረን መገልገል እንፈልጋለን እና ይፈቀድልን" ብለው ጠይቀው፣ ከሁለቱ ጽላት በቀር ሌላ አልተፈቀደም ብሎ መልስ የተሰጠበት ቦታ የለም።

ያም ሆነ ይህ በሐዲስ ኪዳንም በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በአብ፤ በወልድ፤ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠምቀው፤ ሁለተኛ የድኅነት ልደት ተወልደው፣ የእግዚአብሔር ልጆች እንዲሆኑ ሥልጣን ሰጣቸው። ለክርስቲያኖችም ከፀሐይ መውጫ እስከ ፀሐይ መግቢያ ድረስ እንደሚበዙና በአዲስ ኪዳን በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንጹሕ የሆነውን ቍርባን ከኢየሩሳሌም ውጭ በየቦታው ለእግዚአብሔር ማቅረብ እንደሚችሉ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል።

1. "ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ይከበራልና፤ በየስፍራው ለስሜ ዕጣን ያጥናሉ፤ ንጹሕንም ቍርባን ያቀርባሉ፤ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይሆናልና ይላል ሁሉን የሚችል እግዚአብሔር" ሚል 1፥11።

2. "ቤቴ ለአሕዛብ ሁሉ የጸሎት ቤት ትባላለች ተብሎ ተጽፎ የለምን? እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችኋት ብሎ አስተማራቸው" ማር11፥17፤ ኢሳ 56 ፥ 7፤ ኤር 7፥11።

ይህ ትንቢት በቀጥታ ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች መሆኑ ግልጥ ነው። ምክንያቱም በብሉይ ኪዳን ቤተ መቅደስም ሆነ የዕጣን፣ የቁርባን አገልግሎት እንኳን ከፀሐይ መውጫ እስከ ፀሐይ መግቢያ ድረስ ላሉ አሕዛብ፣ በኢየሩሳሌም ከሚኖሩ የእግዚአብሔር ሕዝብ በቀር ለእስራኤል ጎረቤት አገሮች እንኳ አልተፈቀደምና። ነቢዩ ሚልክያስ ንጹሕ ዕጣን ያለው በማቴ 2፥11 ወንጌል እንደተናገረው፣ ከአሕዛብ ወገን የሆኑ ሰብአ ሰገል፣ በቤተልሔም ዋሻ ለክርስቶስ ካቀረቡት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በዓለም ያለን ክርስቲያኖች በክርስቶስ ስም ለክርስቶስ የምናቀርበው ቅዱስ ዕጣን ነው።

ንጹሕ ቍርባን የሚለውንም በማቴ 26፥26 ጌታ ኅብስቱን አንሥቶ "ነገ የሚቆረሰው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ወይኑንም አንሥቶ ነገ ስለብዙዎች ኃጢአት የሚፈስሰው ደሜ ይህ ነው" ብሎ ለሐዋርያት የሰጣቸው የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው። ንጹሕ የተባለው ርሱ በባሕርዩ ንጹሕ ሆኖ የእኛን የኃጢአት እድፍ ስለሚያነጻ ነው።

በብሉይ ኪዳን በኢየሩሳሌም ብቻ መሆን የሚገባቸው ቤተ መቅደሱ፤ ዕጣኑ፣ ቁርባኑ፣ በክርስቶስ ደም በአዲስ ሕይወት፣ በአዲስ ተፈጥሮ፤ በአዲስ ሥርዓት፣ ክርስቲያኖች ለሆንን ለዓለም ሕዝብ በየሥፍራው (በያለንበት) እንድንጠቀምባቸው ከተፈቀዱልን፣ በኢየሩሳሌም ይኖሩ የነበሩት ሁለቱ ጽላት ከፀሐይ መውጫ እስከ ፀሐይ መግቢያ ተባዝተው በዓለም ያለን ክርስቲያኖች በያለንበት በየቤተ መቅደሳችን ለሥጋውና ለደሙ የክብር ዙፋንነት ብንገለገልባቸውና የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ብናከብርባቸው ምን የሚጎዳ ነገር ተገኘ? የሚያስደነግጠውስ ምኑ ነው? ስህተቱስ የቱ ላይ ነው?

እንዲሁም ኣሥርቱ ትእዛዛት የተጻፉባቸው ሁለቱ ጽላት መባዛት፣ መራባት የለባቸውም ከተባለ፣ "በጽላቱ ላይ የተጻፉት ኣሥርቱ ትእዛዛት መባዛት የለባቸውም፣ ከኢየሩሳሌምም መውጣት የለባቸውም" ማለት አይደለምን? ትእዛዛቱም ተከለከሉ ማለት ነውና።

በጽላቱ ላይ የተጻፉት ትእዛዛት በእግዚአብሔር ፈቃድ ከፀሐይ መውጫ እስከ ፀሐይ መግቢያ ድረስ በሚገኙ ክርስቲያኖች እጅ ገብተዋል። ይህም ያስደስታል እንጂ አያሳዝንም። ይህ ከሆነ ለሥጋውና ለደሙ (ለክርስቶስ) ክብር ሲባል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚገኙ ጽላት ምን በደል አስከተሉ? እግዚአብሔር ለቀደሙ አባቶቻችን በታቦቱ አድሮ የሠራላቸውን ድንቅ ሥራ እያስታወስን፣ እግዚአብሔርን ከማመስገን ውጭ? ደግሞም ጌታ ስለ ጸሎት ሲያስተምረን "አባታችን ሆይ!..." በሚለው ጸሎት ውስጥ "ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች፣ እንዲሁም በምድር ትሁን..." በሉ ብሏል። በዚህ መሠረት፣ በዮሐንስ ራዕይ 11፥19 ላይ ታቦቱን በሰማይ አሳይቶናል። ስለዚህ የሙሴ የቃል ኪዳኑ ታቦት በሰማይ እንዲገኝ፣ በሰማይ እንዲሆን፣ በሰማይ እንዲታይ ፈቃዱ ከሆነ፣ በምድርም እንዲሆን ፈቃድህ ይሁን ብለን ብንጠቀምበት ስህተቱ ምንድን ነው?

ጥያቄ 3፦ የሰሎሞን ቤተ መቅደስ እስኪሠራ ድረስ፣ በርግጥ ታቦቱ ከቦታ ወደ ቦታ ይዘዋወር ነበር፤ ቤተ መቅደሱ ተሠርቶ ታቦቱ ወደ ቤተ መቅደሱ ከገባ በኋላ ግን ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው ስለመውጣታቸው መጽሐፍ ቅዱስ አይናገርም። ታዲያ ዛሬ ክርስቶስ ደሙን ካፈሰሰ በኋላ፣ በብሉይም ሆነ በሐዲስ ኪዳን መመሪያ ሳይኖር፣ ከየት አምጥታችሁ ነው ታቦትን በየጊዜው በማውጣት የክርስቲያኖች ኅሊና ሁሉ ወደተሰቀለው ክርስቶስ መሆኑ ቀርቶ ወደ ታቦቱ የሆነው?

መልስ፦ በብሉይ ኪዳን እንኳን አይወጣም ነበር ማለት አንችልም። ምክንያቱም በችግራቸው ጊዜ ለችግራቸው መፍትሔ ያገኙ ዘንድ ከነበረበት ከድንኳኑም ቢሆን ያወጡት ነበርና ለምሳሌ፦

1. በሙሴ ምትክ የተመረጠ ኢያሱ ሕዝበ እስራኤልን እየመራ ወደ ምድረ ርስት ሲሄድ፣ ድንገት የዮርዳኖስ ወንዝ ሞልቶ ባገኘው ጊዜ፣ ወንዙን ከፍሎ ሕዛቡን ለማሻገር ከእግዚአብሔር በተነገረው መሠረት፣ ካህናቱ ታቦቱን ከነበረበት ቦታ ተሸክመው ወደ ወንዙ በመሄድ፣ ታቦቱን የተሸከሙት ካህናት እግር ወንዙን ሲረግጥ፣ ወንዙ ተከፍሎ ሕዝቡ ሁሉ በሰላም መሻገራቸውን እናገኛለን፤ ኢያሱ 3፥1-17።

2. እስራኤል ምድረ ርስት በደረሱ ጊዜ፣ ምድረ ርስት (ኢያሪኮ) በጠላት እጅ በጽኑዕ ግንብ ታጥራ አገኟት። በዚህም ጊዜ ይህን የጠላት የግንብ አጥር ለማፍረስና ርስታቸውን በእጃቸው ለማድረግ፣ እግዚአብሔር የገለጠላቸው ጥበብ፣ ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው፣ ሕዝቡም እየተከተሉ ሰባት ጊዜ ግንቡን እንዲዞሩት ነው። የታዘዙትን አደረጉ ግንቡም ፈረሰላቸው፤ ኢያሱ 6፥1-17።

3. እስራኤል ጠላት በበረታባቸው ጊዜ ጠላትን ለማሸነፍ ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው ይወጡ ነበር፤ 1ሳሙ 5፥1-ፍ። ስለዚህ በብሉይ ኪዳን ካህናቱ ታቦቱን ከቦታ ወደ ቦታ ሲንቀሳቀሱ ካልሆነ በቀር ለሚፈልጉት ዓላማ ታቦቱን ካለበት ቦታ ተሸክመው አያወጡትም ነበር ማለት አንችልም። ሰሎሞን ቤተ መቅደሱን ሠርቶ ካስገባው በኋላ ቢሆንም ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው እንዳያወጡ የሚል ሕግም የለም። እግዚአብሔር የሠራው ሥራ፣ በብሉይ ኪዳን የተፈጸመው አገልግሎት ሁሉ ሙሉ በሙሉ በመጽሐፍ ቅዱስ አልተጻፈም። በመጽሐፍ ቅዱስም ያልተጻፈ ብዙ ነገር እንዳለ እናምናለን፣ ከዚህ በመነሳት ነው እኛ በሐዲስ ኪዳን ታቦትን ተሸክመን የምናወጣው፦

በብሉይ ኪዳን በእግዚአብሔር ቸርነት (ትእዛዝ) ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው እንዲወጡ ተደርጎ ካህናቱም ታቦቱን ተሸክመው በመውጣት በታቦቱ ያደረ ኃይለ እግዚአብሔር ለሕዝበ እስራኤል ያደረገውን ድንቅ ሥራ ለማሰብና እግዚአብሔርን ለማመስገን ነው። ዛሬም ለሥጋና ለደሙ የክብር ዙፋን የሆነውን፣ ቅዱስ ስሙም የተጻፈበትን ቅዱስ ታቦት በምናወጣበት ጊዜ፣ በደሙ የባረከን መድኅነ ዓለም ክርስቶስ አሁንም የሥጋውና የደሙ ዙፋን በሆነው በታቦቱ ረቂቅ ኃይሎች በማስተላለፍ በረከቱን ያበዛልናል ብለን በማመን ነው።

የተሰቀለው አምላክ መክበሩና መንገሡ ቀርቶ በየጊዜው ታቦት ወጣ እየተባለ፣ ታቦቱ ብቻ ነገሠ፣ ከበረ፣ ሕዝቡም ወደ አምልኮ ባዕድ ኮበለለ ስለሚለው ግን አንድ ሕዝብ የንጉሡን ዙፋን ሲያከብርና ሲፈራ ንጉሡን ማክበሩና መፍራቱ እንደሆነ መዘንጋት የለበትም።

እኛ የምናምነው ቅዱስ ስሙ የተጻፈበትን የክርስቶስ ሥጋና ደም፣ የክብር ዙፋን የሆነውን ታቦት ማክበራችን. በኪሩቤል ዙፋን የሚቀመጥ መድኅነ ዓለም ክርስቶስን ማክበራችን መሆኑን ነው። በታቦቱ ፊት መስገዳችንም በታቦቱ ለተጻፈው ለቅዱስ ስሙ ነው። በታቦት ፊት ለእግዚአብሔር ስም ይሰግዱ የነበሩ ኢያሱና የእስራኤል ሽማግሌዎች በረከት አገኙበት እንጂ አልተጎዱበትምና ነው፤ ኢያ 7፥6፣ ዘዳ 33፥10።

በሐዲስ ኪዳንም "ድል ለነሣው ስውር መናን እሰጠዋለሁ፤ የብርሃን መጽሐፍንም እሰጠዋለሁ፤ በዚያ መጽሐፍ ውስጥ ላይ ከተቀበለው በቀር ማንም የሚያውቀው የሌለ አዲስ ስም ተጽፎበታል" ራዕ 2፥17። ለዚህ ስም ደግሞ ጉልበት ሁሉ መንበርከክ እንደሚገባው መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ "ይህም በሰማይና በምድር፣ በቀላያትና ከምድርም በታች ያለ ጉልበት ሁሉ ለኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሰግድ ዘንድ ነው። አንደበትም ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሔር አብ ክብር፣ ጌታ እንደሆነ ያምን ዘንድ ነው"፤ ፊልጵ 2፥10-11። በዚህ መሠረት ቅዱስ ስሙ በተጻፈበት (ከነጭ ድንጋይ፣ ከእብነ በረድ፣ ከእንጨት በተሠራው) በጽላቱ ፊት ለቅዱስ ስሙ መስገድ ታላቅ የመንፈስ ጥበብ እንጂ ሞኝነት አይደለም። ምናልባት ስለታቦት፣ ስለጽላት ባለማወቅ ባጠቃቀሙ በኩል የሚሳሳቱ አባቶችን፣ እናቶችን፣ ወንድሞችንና እህቶችን በተገቢው መንገድ ማስተማር ተገቢ ነው።

ከዚህ በላይ ስለ ታቦት ከቤተ መቅደስ መውጣትና አለመውጣት መፅሐፍ ቅዱሳዊ ከመሆኑም በተጨማሪ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሆኑ መታወቅ አለበት።

ብዙዎች በሐዲስ ኪዳን ታቦትን ለመቃወም በኤር 3፥16 የተጻፈውን ጠቅሰው “በዚያ ዘመን፦ የእስራኤል ቅዱስ፣ እግዚአብሔር፣ የቃል ኪዳኑ ታቦት፣ እነኋት እያሉም በአፋቸውም አይጠሯትም፣ ከእንግዲህ ወዲህ አይሿትም” ተብሏልና ታቦት አያስፈልግም በማለት ያስተምራሉ።

እንደተባለው ታቦት ብሎ መጥራት ካላስፈለገ፣ በኤርምያስ 31፥34 ደግሞ፦ እያንዳንዱ ሰው ባልንጀራውን፣ እያንዳንዱም ወንድሙን፦ "እግዚአብሔርን ዕወቅ ብሎ አያስተምርም” ተብሎ ስለተጻፈ፣ እንግዲህ ሰው ሁሉ በየዘመኑ እግዚአብሔርን እንዲያውቅ ማስተማር አያስፈልግም ማለት ነዋ! ደግሞም ጌታችን በማቴ 28፥19 “እንግዲህ ሒዱና በአብ፣ በወልድና፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው አሕዛብን ሁሉ አስተምሩ” ብሎ መናገሩ ስህተት መሆኑ ነዋ! በአጠቃላይ እንዲህ ነው ብሎ ከመናገር አስቀድሞ በመጽሐፍ የተጻፈው ነገር ለምንና እንዴት ባለ ሁኔታና ጊዜ መፃፉን ማጥናትና መልእክቱን (ምስጢሩን) መመርመር ይገባል እንላለን።

በመጨረሻ ግን በኢትዮጵያ ኦርቶኮክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማርያም፣ የቅዱሳን፣ የሰማዕታት፣ የመላዕክት፣ ወዘተርፈ ታቦት እየተባለ የተሰየመበት ምክንያቱና የዚህ ስያሜ ከየት ነው የመጣው? ምንድን ነው? የሚሉ ጥያቄዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ እርግጥ ነው።

እንዲህ ተብሎ መሰየሙ በትንቢተ ኢሳይያስ 56፥46 በተገለጸው መሠረት የእግዚአብሔርን ሰንበቱን ለሚጠብቁ፣ ደስ የሚያሰኘውንም ለሚመርጡ፣ ቃል ኪዳኑንም ለሚይዙ ጃንደረቦች (ስለእግዚአብሔር መንግሥት ራሳቸውን ጃንደረባ ያደረጉ ቅዱሳን) ማቴ 19፥12 በእግዚአብሔር ቤትና በቅጥሩ የዘለዓለም መታሰቢያ እንደሚደረግላቸው የተገለጠ በመሆኑ፣ ይህን አብነት በማድረግ ጌታ ሥጋውና ደሙ የሚከብርበት ሆኖ ለቅዱሳኑም መታሰቢያ ለማድረግ ነው፤ (መዝ 111፥7)። እንዲሁም የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነውና፤ ምሳ 10፥7። በዚህ ምክንያት እንጂ በታቦቱ የሚከብረው መድኃኒተ ዓለም ክርስቶስ መሆኑ ግልጽ ሊሆን ያስፈልጋል። እግዚአብሔር አስተዋይ ልቡና ይስጠን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።

አለባበስ

“ሴት የወንድን ልብስ አትልበስ፣ ወንድም የሴትን ልብስ አይልበስ፣ ይህን የሚያደርግ በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ነው” ዘዳ. 22፡5። ስለ አለባበሳችን እንወያያለን። ዛሬም እህቶቻችን ላይ እናተኩራለን፥ ምነው እኛ ላይ ብቻ እንደማትሉኝ ተስፋአለኝ። ስለአለባበስ መነጋገር ያስፈለገን እውነተኛ ክርስቲያን በአነጋገሩ፣ በአረማመዱ፣ በአመጋገቡ፣ በአለባበሱ፣ ብቻ በሁሉ ነገሩ የተለየ መሆን ስላለበት ነው።

ይኸውም ሁሉን በአግባብና በሥርዓት ስለማድረግ ነው። እህቶቻችን ላይ ማተኮር ያስፈለገው ደግሞ፦ በአብዛኛው በዚህ ረገድ ትችት የሚበዛው በእነርሱ ላይ ስለሆነ ነው። እነሆ ውድድሩ ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረና እየከፋ ነው። ለመልካም ነገር መወዳደር ባልከፋ፣ ነገር ግን በከተማችን በተለይም በዋና ዋና መንገዶች ላይ የምናየው የእህቶቻችን አለባበስ፣ አንዷ ከሌላዋ ልቃና በልጣ ለመታየት የሚደረግ ግብግብ እንደሆነ መገመት አያዳግትም።


እናቶች ይህንን ጊዜ አታሳየን ብለው ሲጸልዩ

በርግጥ እህቶቻችን በዚህ እንደማይስማሙ እናውቃለን፤ አብዛኞቹም ስለተመቸኝና የምወደው ዓይነት አለባበስ ስለሆነ ነው እንዲህ የምለብሰው ይሉናል። ይሁን እንጂ እውነቱ ሌላ ይመስላል ምክንያቱም፦

  • ብርድ ልብስ ለብሰን እንኳን በማንቋቋመው የብርድ ወቅት ሰውነትን በቅጡ የማይሸፍን ብጣሽ ጨርቅ ጣል አድርጎ መውጣት እንዴት ያለ ምቾት ነው?
  • እጅግ አስጨናቂ ሙቀት ባለበት ሰዓት ሰውነት ላይ ተጣብቆ ሌላ ጭንቀት የሚፈጥር አለባበስ እንደምን ብሎ ያስደስታል?

ዓላማችን ምንም ይሁን ርሱ ላይ የመከራከር ፍላጎት የለንም። ነገር ግን አለባበሳችንን እንደ ክርስቲያን እንፈትሸው ዘንድ ይገባልና መሰልጠን ይሁን ወይስ መሰይጠን? ልንለየው ይገባናል። አብዛኞቹ ሴቶች ይህን ተግባር ስልጣኔ እንጂ ስህተት ነው ብለው አያምኑም። ለእነዚህ ሴቶች ከሃይማኖት ብቻ ሳይሆን ከባሕላችን ጭምር ያፈነገጠውን የምዕራባውያንን አለባበስ መልበስ ዘመናዊነት ነው። ☛ላንቺስ?☚ መጽሐፍ ቅዱስስ ምን ይላል?

ማንኛዋም ሴት የሰውነቷን ቅርፅ የሚያሳይ ወይም ክፍትፍት ልብስ ለብሳ በመሄዷ የሁሉንም ወንዶች ስሜት መፈታተኗ ርግጥ ከመሆኑም በላይ፣ በመንፈሳዊ ሕይወት ደካማ የሆኑትን ደግሞ ለኃጢኣት አጋልጦ ይሰጣል። እዚህ ላይ የተሳሳተው በራሱ ደካማነት ነው ብሎ ምክንያት መስጠት አይቻልም። እግዚአብሔር የሚጠይቀው "በማን ተሰናከለ?" የሚለውን ጭምር ነውና። በክርስትና ደግሞ ሰውን ማሰናከል እጅግ የከፋ ኃጢኣት ነው። “ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ይሻለው ነበር” ማቴ 18፥6።

አንዳንድ ሴቶች እግዚአብሔር "ምን ሠራሽ?" እንጂ "ምን ለበስሽ?" አይለኝም፣ ይላሉ። እግዚአብሔር ግን እንዲህ ይላል፦ “እንግዳ ልብስ የሚለብሱትንም ሁሉ እቀጣለው” ትን ሶፎ 1፥18። እንግዲህ የሴቶቹን እንቀበል? ወይስ የእግዚአብሔርን? ምርጫው ያንቺው ነው እህቴ። መፅሐፍ ግን እንዲህ ይላል፦ “ከስው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባል” የሐዋ 5፥29። በሴቶችና በወንዶች መካከል የአለባበስ ልዩነት ሊኖር ይገባል። “ሴት የወንድን ልብስ አትልበስ፣ ወንድም የሴትን ልብስ አይልበስ፣ ይህን የሚያደርግ በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ነው” ዘዳ 22፥5። ታዲያ ቀሚስን የወንድ፣ ሱሪን የሴት ማን አደረገው? ይህ የሰነፍና ለስህተታቸው ምክንያትን የሚሹ ሴቶች የሚያነሱት ጥያቄ ነው። በመጀመሪያ ደረጃ እኛ ኦርቶዶክሳውያን የእግዚአብሔርን ቃል ዓውቀን ልንፈፅመው እንጂ በቃሉ ላይ የምንፍቅና ጥያቄ እናነሳ ዘንድ ተገቢ አይደለም። ግን ደግሞ ተፈጥሯችንን ብቻ በማየት ኅሊናችን ራሱ ቢናገር ሱሪ የሴት ነውን? ቀሚስስ የወንድ ነው እንዴ? “ተፈጥሮ እንኳን አያስተምራችሁምን?" 1ኛ ቆሮ 11፥14። “ዳሩ ግን ማንም ሊከራከር ቢፈቅድ እኛ ወይም የእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት እንዲህ ያለ ልማድ የለንም” 1ኛ ቆሮ 11፥16። ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው ስህተት መሆኑን መናገር እንጂ መከራከር አያስፈልግም፣ ክርስትና በምርጫ ነውና። “በፊትህ እሳትና ውኃን አኑሬአለው፥ ወደ ወደድኸው እጅህን ክተት” ሲራ 15፥15። ከዚህ ላይ ግን ቀሚስ ሲባል ከውስጥ ሱሪ የማይሻለውን ብጣሽ ጨርቅ እንዲሁም ቁመቱ ረዥም ሆኖ ከሰውነት ጋር የሚጣበቀውን ዓይነት አለባበስ ማለት እንዳልሆነ ልብ እንበል።

እህቶቻችን ሆይ ማስተዋልን ትላበሱ ዘንድ እንለምናችኋለን። መሰልጠንን እና መሰይጠንንም ትለዩ ዘንድ ይሁን። ሰውነትሽ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ነውና፣ ሁሉን በአግባብና በሥርዓት አድርጉለት። ደግሞም ክርስትና ራስ ወዳድነትን አብዝታ ትጠላለች፥ ምንም ነገር ስናደርግ ስለ ሌላው ሰው ልናስብ ያስፈልገናል። እኛስ ሰውን ወደ ዝሙት ሊያመራው ስለሚችል አለባበሳችን እጅግ ተጨነቅን፣ ነገር ግን ቅዱስ ጳውሎስ ወንድማችንን ስለማሰናከል ምን አለ? “መብል ወንድሜን የሚያሰናክለው ከሆነ ወንድሜን እንዳላሰናክለው ለዘለዓለም ከቶ ሥጋ አልበላም” 1ኛ ቆሮ 8፥13።

እንግዲህ ክርስትና እዚህ ድረስ ነው፥ ስለራሳችን ብቻ ሳይሆን ስለ ወንድሞችና እህቶች የምናስብባት። ለእነርሱም መሰናከያ እንዳንሆን እየተጠነቀቅን ሁሉን በአግባብና በሥርዓት የምናደርግባት፤ እምነታችንን በምግባር የምንገልጽባት ናት። “በእውኑ ኢትዮጵያዊ መልኩን፣ ነብር ዝንጉርጉርነቱን ይለውጥ ዘንድ ይችላልን?" ትን ኤር 13፥27። እህቴ ሆይ አንቺም ኤርምያስ እንዳለው ኢትዮጵያዊነትሽን ጠብቂ። የምዕራባውያን በዓል ከሆነው አለባበስም ሆነ የምንዝር ጌጥ ራስሽን አርቀሽ በሚያኮራው ኢትየጵያዊ ባሕላችን ትዋቢ ዘንድ እግዚአብሔር ይርዳሽ። ስለእውነት አሁን ማን ነው ተጠያቂ፣ የጡት ካንሰር ቢይዘን? አረ እንዲያው ለመሆኑ ስንቶቻችን የጡት ካንሰር፣ የዲስክ መንሸራተት፣ የማኅፀን ካንሰር፣ እንዲሁም ሌሎች የበሽታ ጠንቆች የሚመጡብን በዚህ አለባበሳችን እንደሆነ አስበነው እናውቅ ይሆን?

ሕገ ኦሪት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ለምንድነው ኤዲት የሚደረገው

ፊደል[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የውጭ መያያዣዎች እና ዋቢ መጻሕፍት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ከሉሌ መልአኩ፤ ሦስተኛ እትም - ፲፱፻፹፮ ዓ.ም.

በ"Wikimedia Commons"
(የጋራ ፎቶዎች ምንጭ)
ስለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሚገኛኙ
ተጨማሪ ፋይሎች አሉ።