የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በኢትዮጵያ መንግስት የበላይ ጠባቂነት የሚንቀሳቀስ የሀገሪቱ ብቸኛ የቴሌቪዥን ጣቢያ ነው። ዜና፣ ስፖርት፣ ሙዚቃ፣ እና የመሳሰሉትን ስርጭቶች ለተመልካቾች ያቀርባል። ስርጭቱንም በአማርኛ፣ በትግርኛ፣ በኦሮምኛ፣ በሶማልኛ፣ በአፋርኛ፣ በእንግሊዝኛ እና በአረብኛ ቋንቋዎች ያቀርባል።
መቀመጫውን አዲስ አበባ ከተማ ያደረገ በአሁኑ ጊዜ ድርጅቱ በኢ.ቴ.ሬ.ድ. (የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እና ሬዲዮ ድርጅት) ስር የሚተዳደር ነው።
-