Jump to content

ዋይት ሃውስ

ከውክፔዲያ
የኋይት ሃውስ ደቡባዊ ገፅ

ኋይት ሃውስአሜሪካ ዋና ከተማ ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኝ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የመኖሪያ እና መደበኛ የስራ ቦታ ነው። ይህ ቤት የተገነባው ከ1792 እስከ 1800 እ.ኤ.አ. ባሉት አመታት ሲሆን የገነባውም የአየርላንድ ተወላጅ በሆነው አርኪቴክት ጀምስ ሆባን (James Hoban) ነበር። ቤቱ ከጆን አዳምስ (John Adams) ጀምሮ ለሁሉም የአሜሪካ ፕሬዝዳንቶች መኖሪያ የሆነ ሲሆን ቶማስ ጄፈርሰን (Thomas Jefferson) የተባለው የአሜሪካ 3ኛ ፕሬዝዳንት በ1801 ሲገባ በአርኪቴክት ቤንጃሚን ሄንሪ ላትሮብ (Benjamin Henry Latrobe) ቤቱን ወደውጭ አስፍቶታል።