Jump to content

የሕግ የበላይነት

ከውክፔዲያ

የሕግ የበላይነት ማለት ማናቸውም ሰው ወይም ወኪል በሕጋዊ መሠረት ከሆነ ከሕግ ሥር ተጠቅልሎ ይገኛል። የመንግስት ውሳኔዎች ከታወቁት ሕጋዊና ግብረገባዊ መርኆች ይደርሳሉ የሚል ጽንሰ ሀሣብ ነው። ከሕጉ በላይ የሆነ የለም ይላል። የሕገ መንግሥት ታሪክ እንዳሳየን ይህ መርኅ ከጥንት ጀምሮ ታውቋል። አሪስጣጣሊስም እንደ ጻፉ፣ «ከዜጎች ማንም ሰው ከመግዛት ይልቅ ሕጉ እንዲገዛ ይገባል።»