ሴባስቶፖል መድፍ

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስከረመ 21 1867 ጋፋት ደበረታቦር የተመረቀው ሴባስቶፖል መድፍመቅደላ ላይ

ሴቫስቶፖል መድፍዓፄ ቴወድሮስ ዘመን በአውሮጳውያን ሚሲዮን መሪነትና በኢትዮጵያውያን ቀጥቃጮች ረዳትነት ጋፋትደብረ ታቦር እ.ኤ.አ መስከረም 21፣ 1867 ተሰርቶ የተመረቀው መድፍ ነው። ስሙ የተወሰደው በክሪም ከሚገኘው ሴባስቶፖል ከሚባለው ከተማ ነው። ለጦርነት እንዲውል አውሮጳውያኑን እራሳቸውን ባስደነቀ የአመራር ችሎታ ንጉሠ ነገሥቱ መንገድ እያሰሩ በራሳቸውም እጅ ድንጋይ ቋጥኝ እየፈነቀሉ ከደብረ ታቦር መቅደላ በ10 ቀን ያጓጓዙት መድፍ ነበር። ሆኖም ግን አፈ ጠባብ ስለነበር አንድ ጊዜ እንደተኮሰ መድፉ ፈንድቶ ከጥቅም ውጭ ሆነ።