ሱመር

ከWikipedia

(ከሹመር የተዛወረ)
ዘልለው ለመሐድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
የሱመር ዙሪያ

ሱመር (ወይም ሹመር፣ ሳንጋር፣ ሰናዖር) በጥንታዊ መካከለኛ ምሥራቅ አለም በቅድሚያ ሥልጣኔ የሚባል ኹኔታ የደረሰለት አገር ነበር። ዘመኑ ከታሪካዊ መዝገቦች መነሻ ጀምሮ ይታወቃል። 'ሱመራዊ' ማለት ሱመርኛ የቻሉ ወገኖች ሁሉ ነው። ከጥንታዊ ግብፅ እና ከሕንዶስ ወንዝ ሸለቆ ሥልጣኔ ጋራ ከሁሉ መጀመርያ ሥልጣኔ ካሳዩት አገሮች አንዱ ነው ይባላል።

[ለማስተካከል] ስም

ሹመሩ የሚለው ስም በጎረቤቶቻቸው በአካድ ሰዎችም ሲጠራ ሕዝቡ ለራሳቸው የነበራቸው ስም ሳግ-ጊ-ጋ (ጥቁር ራስ ያላቸው) ነበር። አገራቸውንም ኪ-ኤን-ጊር ይሉት ነበር። በተረፈ በኬጢያውያን መዝገቦች አገሩ ሳንሃር፣ በግብጽ አማርና ደብዳቤዎች ሳንጋር፣ በመጽሐፍ ቅዱስሰናዖር ይባላል።

[ለማስተካከል] ታሪክ

የኡር ንጉሥ መስካላምዱግ ራስ ቁር

ጽሕፈት በመፍጠሩ የታሪክ መጋረጃ ሲከፈት፣ ሱመራውያን በደቡብ ሜስጶጦምያ (ከጤግሮስኤፍራጥስ ወንዞች መኃል፣ የዛሬው ኢራቅ) ይገኙ ነበር።

ጥንታዊው የሱመራውያን ነገሥታት ዝርዝር የያንዳንዱን ከተማ ሥርወ መንግሥት ይዘርዝራል። ከነዚህም በመግቢያው ያላቸው ነገሥታት ከማየ አይህ በፊት እንደ ነገሡ ይላል። እነዚህ ስሞች ትውፊታዊ ሊሆኑ ይችላል። ከሌላ አፈ ታሪክ ምንጭ የታወቀው በዝርዝሩ የተገኘ ስም የኪሽ ንጉሥ ኤታና ነው። ከዚያ በኋላ የኤንመርካርና የልጁ ልጅ የጊልጋሜሽ ስሞች ይታያሉ። እነዚህ በኡሩክ እንደነገሡ ይገልጻል። ከሥነ ቅርስ የታወቀው መጀመርያ ስም ኤላምን ያሸነፈው የኪሽ ንጉሥ ኤንመባራገሲ ነው። እሱ ደግሞ የጊልጋሜሽ ትውፊት በተባለ ጽሑፍ ስለሚገኝ ይህ ለጊልጋሜሽ ታሪካዊ ሕልውና ምናልባትነት መስጠቱ ይታመናል።

የኡሩክ ንጉሥ ኤንሻኩሻና ሐማዚን፣ አካድን፣ ኪሽንና ኒፑርን በማሸነፉ መጀመርያ 'የሱመርና የአካድ ንጉሥ' የተባለ ነበረ። በኋላ የአዳብ ንጉሥ ሉጋል-አኔ-ሙንዱ በዘመቻ እስከ ሜዲቴራኔያን እና እስከ ጣውሮስ ተራሮች (ትንሹ እስያ) ና እስከ ዛግሮስ ተራራዎች (ፋርስ) ድረስ እንዳቀና ይመዘገባል። ከዚህ በኋላ የላጋሽ ንጉሥ ኤ-አና-ቱም ሱመርን ሁሉ ኤላምንም በከፊል አሸንፎ እሱ ላይኛ ንጉስ ሆነ። ከተገኙ ጽላቶች መሠረት፣ የሱ መንግሥት አደራረግ ተገዥ ወገኖችን ማስፈራራትና ግፍ መሆኑን ልንገምት እንችላለን። የላጋሽ ንጉሥ ኡሩካጊና የራሱን ሕገጋት አውጥቶ ለድኆች ማሻሻል አደረገ፤ በተጨማሪ 1 ሚስት ቀድሞ ብዙ ባሎችን የምታገባበትን ልማድ ከለከለ።

የሉጋል-ዛገ-ሲ መንግሥት (ቀይ)

ከዚያ ቀጥሎ የኡማ ንጉሥ ሉጋል-ዛገ-ሲ ላጋሽን አገለበጠውና ዋና ከተማውን በኡሩክ አድርጎ መንግስቱን ከፋርስ ወሽመጥ እስከ ሜዲቴራኔያን ድረስ እንደ አስፋፋ በጽላቶች ተቀርጿል።

ከሉጋል-ዛገ-ሲ ላይኛነቱን የያዘ ሱመራዊ ሰው ሳይሆን የአካድ ንጉሥ 1 ሳርጎን ነበር። የአካድ ሰዎች ሴማዊ ቋንቋአካድኛ ይናገሩ ነበር። ቋንቋቸውን በሱመር እንዲሁም በኤላም ይፋዊ በግድ አደረጉ። በጽላት ዜና መዋዕል መዝገቦች መሠረት፣ ሳርጎን የባቢሎንን ሥፍራ ወደ አካድ ዙሪያ አዛወረ።

የአካድ መንግሥት በጉታውያን ዕጅ ከወደቀ በኋላ የላጋሽ ንጉሥ ጉዴአ ተነሣ። ከዚያ በኋላ የኡር ንጉስ ኡር-ናሙ ላጋሽን አሸንፎ ላይኛነቱን ያዘ። እሱ በተለይ የኡር-ናሙ ሕገጋት ስለ ተባለው ፍትኅ ይታወሳል። በዚህ ወቅት ብዙ ሴማዊ ቋንቋ ያላችው አሞራውያን ወገኖች ወደ ሜስጶጦምያ ስለ ገቡ፣ የሱመርኛ ጥቅም ቀስ በቀስ ቀነሰ። ሆኖም ሱመርኛ በትምህርት ቤትና በሃይማኖት ረገድ ይቀጠል ነበር።

ይህ የኡር መንግሥት እስከ 2012 ክ.በ. ኤላማውያን እስከ ወረሩት ድረስ ቆየ። የዚያ ውጤት አሞራውያን ለራሳቸው ከተሞች ያዙና የሱመር ሃይል ጠፋ። ከነዚህ ከተሞች መካከል ባቢሎን በንጉስዋ ሃሙራቢ ወቅት ላይኛነቱን ለረጅም ወራት መሰረተች።

የኔ መሣርያዎች