ቤስጳስያን

ከውክፔዲያ
የቤስጳስያን ምስል

ቤስጳስያን (ሮማይስጥ፦ Titus Flavius Vespasianus /ቲቱስ ፍላዊዩስ ዌስፓሲያኑስ/) (ከ2 ዓ.ም. እስከ 71 ዓ.ም. የኖሩ) ከታህሳስ ወር 62 ዓ.ም. እስከ 71 ዓ.ም. የነገሡ የሮሜ መንግሥት ቄሣር ነበረ።

60 ዓ.ም. ሰዶማዊው ቄሣር ኔሮን ራሱን ከገደለ ቀጥሎ፣ የሮሜ መንግሥት በብሔራዊ ጦርነት ተያዘ። በየክፍላገሩ ሠራዊቶቹ የወደዱትን አለቃ ሾመው፣ በ1 አመት ብቻ ውስጥ የሮሜ ሴናት (ሕግ አዋሳኝ ቤት) በ4 ልዩ ልዩ ነገሥታት ላይ ዘውዱን ለመጫን ተገደደ። ይህ «የአራቱ ቄሣሮች ዓመት» ይባላል። ከነዚህም፣ መጀመርያ 3ቱ ጋልባኦቶ እና ቬቴሊውስ ሁላቸው ሰዶማውያን አለቆች ነበሩ። በመጨረቫ ግን አንድ ቀና አለቃ ቤስጳስያን አሸነፈና ከዚያ ጀምሮ ነገሠ።

እነዚህ ነገሥታት ሁላቸው በጣም ጨካኝ አለቆች ነበሩ። ቤስጳስያን ደግሞ ኢየሩሳሌምንና መቅደሱን በልጁ ቲቱስ እጅ በማጥፋቱ ይታወቃል። በተለይ ስለ ዳዊት የሆነ አንድ ትንቢት ፈርቶ የዳዊትን ልጆች በየአገሩ አሳደዳቸው።