ኃይሌ ገብረ ሥላሴ
ከውክፔዲያ
ኃይሌ ገብረ ሥላሴ በሚያዝያ 10 ቀን 1965 ዓ.ም. በአሰላከተማ ፣አርሲ ክ/ሃገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጂም ርቀት ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ10ሺ በ5ሺ በግማሽ ማራቶንና በማራቶን እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ11 በላይ የዓለም ሪኮርድ ሰብሮአል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ33 ዓመት ዕድሜው 2 ሰዓት ከ 4 ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ሪኮርድ ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረለላሴ እስካሁን ድረስ 26 የአለም ሪከርዶችን ሰብሯል፡፡ አትሌት ሃይሌ ገብረስላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ10000 ሜትር ወርቅ አስመዝግቡአል።
