ኒው ዮርክ ከተማ

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ኒው ዮርክ ከተማ በሕዝብ ብዛት የአሜሪካ አገር ትልቁ ከተማ ሲሆን 8.4 ሚሊዮን ኗሪዎች ይኖሩበታል። በኒው ዮርክ ክፍላገር ይገኛል።

አውሮፓውያን ከደረሱ አስቀድሞ ጥንታዊ ኗሪዎቹ የለናፔ ወገን ነበሩ። የነሱ ሠፈሮች ካናርሲራሪታንማናሃታ ተባሉ። መጀመርያው የደረሰው አውሮፓዊ በ1516 ዓ.ም. ጆቫኒ ዳ ቬራዛኖ የሚባል ጣልያናዊ ተጓዥ ነበረ። መርከቡ በፈረንሳይ መንግሥት ስም ስለሆነ ስለ ፈረንሳይ ንጉሥ ቦታውን ኑቨል አንጉለም (አዲስ አንጉለም) ሰየመው። ሆኖም አውሮፓውያን መጀመርያ የሰፈሩት የሆላንድ ነጋዴዎች በ1606 ዓ.ም. ነበር። እነርሱ ከ1616 ዓ.ም. ጀምሮ ሥፍራውን ኒው አምስተርዳም (አዲስ አምስተርዳም) አሉት። በ1656 ዓ.ም. እንግሊዞች ያዙትና ስሙን ወደ ኒው ዮርክ (አዲስ ዮርክ) ቀየሩት።

የኔ መሣርያዎች

Variants
Actions
የማውጫ ቁልፎች
ጠቃሚ መሣሪያዎች
በሌሎች ቋንቋዎች