አሰልበርህት

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አሰልበርህት

ልበርህት (552 -608 ዓ.ም.) ከ572 ወይም 582 ዓ.ም. አካባቢ እስከ 608 ዓ.ም. ድረስ የኬንት ንጉሥ ነበረ። ከእንግሊዝ ንገስታትም መጀመርያው የተጠመቀ እሱ ነበር። ስለዚህ በሮማ ካቶሊክ፣ በምሥራቅ ኦርቶዶክስና በአንግሊካን ሃይማኖቶች «ቅዱስ» ይባላል።

አንግሎ-ሳክሶን ዜና መዋዕል ዘንድ፣ እሱ አባቱን የኬንት ንጉሥ ኤዮርመንሪክን ተከተለ። የፍራንኮች ንጉሥ ቻሪበርት ልጅ ቤርታን አገባት። እሷ ክሪስቲያን ነበረችና ከዚህ የተነሣ ንጉሥ ተጠምቆ ክርስትና በእንግሊዝ ሕዝብ መካከል ይፋዊ ሆነ። አውግስጢኖስ ዘካንተርቡሪሮማ588 ዓ.ም. ተልከው የእንግሊዝ ሕዝብ መጀመርያ ሊቀ ጳጳስ ሆኑ።

ልበርህት ከኬንት በላይ በዘመኑ መጨረሻ በሌሎች የእንግሊዝ ደሴት መንግሥታት በኤሴክስምሥራቅ ኤንግላ ላይ ገዥነት ነበረው።

በተጨማሪ በ594 ዓ.ም. ንጉሥ አልበርህት ለአገሩ ሕገ መንግሥት አወጣ። ይህ ሕገ መንግሥት በሮማይስጥ ሳይሆን የተጻፈው በጥንታዊ እንግሊዝኛ ነበረ። በኋላ ዘመን የእንግሊዝ ንጉሥ ታላቁ አልፍሬድ ከዚህ ሕገ መንግሥት ወስደው የተሻሸለ ሕገ መንግሥት አወጡ።

ልበርህት በ608 ዓ.ም. ካረፈ በኋላ ልጁ ኤድባልድ ተከተለው። ኤድባልድ ግን በመጀመርያ ወደ አረመኔነት ቢመልስም በኋላ ግን ክሪስቲያን ንጉሥ ሆነ።