ኢስላማባድ

ከውክፔዲያ

ኢስላማባድ (اسلام آباد) የፓኪስታን ዋና ከተማ ነው። በካራቺ ፈንታ የመንግሥት መቀመጫ እንዲሆን በ1953 ዓ.ም. ተመሠረተ። በ1959 ዓ.ም. መቀመጫው በይፋ ወዲህ ተዛወረ።

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 601,600 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 33°40′ ሰሜን ኬክሮስ እና 73°08′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።