ካርቱም

ከውክፔዲያ

ካርቱም (አረብኛ الخرطوم )የሱዳን ዋና ከተማ ነው።

የካርቱም የመኪና ትራፊክ

የተመሠረተው በ1813 ዓ.ም. በግብጽ ገዥ ሙሐመድ ዓሊ ነበረ። የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር የአካባቢውን ኗሪ ሲጨምር 5,717,300 ሆኖ ሲገመት የራሱ የከተማው ኗሪ ቁጥር ደግሞ 1,397,900 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 15°33′ ሰሜን ኬክሮስ እና 32°32′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።