ዌሊንግተን

ከውክፔዲያ

ዌሊንግተን (Wellington) የኒው ዚላንድ ዋና ከተማ ነው።

ዌሊንግተን ከቪክቶሪያ ተራራ ሲታይ

ማዖሪ ነገድ ከ10ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በሥፍራው ሲኖሩ በማዖሪ ቋንቋ ስሙ ቴ ፋንጋንዊ-አ-ታራ ይባላል። በ1831 ዓ.ም. እንግሊዞች ሠፈሩትና በ1857 ዓ.ም. ዋና ከተማው ከአውክላንድ ወደ ዌሊንግቶን ተዛወረ።

የሚኖርበት ህዝብ ቁጥር የአካባቢውን ኗሪ ሲጨምር 379,000 ሆኖ ሲገመት የራሱ የከተማው ኗሪ ቁጥር ደግሞ 189,700 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 41°17′ ደቡብ ኬክሮስ እና 174°47′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።