ዌስፓሲያኑስ
ከWikipedia
ዌስፓሲያኑስ (ሮማይስጥ፦ Titus Flavius Vespasianus) (ከ2 ዓ.ም. እስከ 71 ዓ.ም. የኖሩ) ከ61 ዓ.ም. እስከ 71 ዓ.ም. የነገሡ የሮሜ መንግሥት ቄሣር ነበረ።
በ60 ዓ.ም. ሰዶማዊው ቄሣር ኔሮን ራሱን ከገደለ ቀጥሎ፣ የሮሜ መንግሥት በብሔራዊ ጦርነት ተያዘ። በየክፍላገሩ ሠራዊቶቹ የወደዱትን አለቃ ሾመው፣ በ1 አመት ብቻ ውስጥ የሮሜ ሴናት (ሕግ አዋሳኝ ቤት) በ4 ልዩ ልዩ ነገሥታት ላይ ዘውዱን ለመጫን ተገደደ። ከነዚህም፣ መጀመርያ 3ቱ ጋልባ፣ ኦጦ እና ዊቴሊዩስ ሁላቸው ሰዶማውያን አለቆች ነበሩ። በመጨረቫ ግን አንድ ቀና አለቃ ዌስፓሲያኑስ አሸነፈና ከዚያ ጀምሮ ነገሠ።
እነዚህ ነገሥታት ሁላቸው በጣም ጨካኝ አለቆች ነበሩ። ዌስፓሲያኑስ ደግሞ ኢየሩሳሌምንና መቅደሱን በልጁ ቲቱስ እጅ በማጥፋቱ ይታወቃል። በተለይ ስለ ዳዊት የሆነ አንድ ትንቢት ፈርቶ የዳዊትን ልጆች በየአገሩ አሳደዳቸው።