የላንካስተር ውል

ከውክፔዲያ

የላንካስተር ውል1736 ዓም በአንዱ ወገን በቨርጂኒያሜሪላንድታላቅ ብሪታንያ ቅኝ አገራትና በሌላው የሆዴነሾኒ ተባባሪነት ወይም ስድስት ብሔሮች የተደረገ ውል ነበረ። ውሉ በአልባኒኒው ዮርክ ተፈጸመ። በዚህ ውል ከሆደናሾኔ ወይም ኢሮኳ ብሔር እና ከቅኝ አገሮቹ መሃል ያለው ወሰን ከበፊቱ ብሉ ሪጅ ተራሮች ጫፍ እስከ ኦሃዮ ወንዝ (በብሪታን ትርጓሜ) ወይም እስከ ኦሃዮ ወንዝ ተፍሳሽ (በኢሮኳ ትርጉም) ድረስ አስፋፋው። በኢሮኳ ዘንድ ሸናንዶዋ ሸለቆ ብቻ ለብር ዋጋ ሸጡ፤ በብሪታንያ ዘንድ ግን ኬንታኪና መላው ምእራብ ቨርጂኒያ ገዝተው ነበር።

ቤንጃሚን ፍራንክሊን የላንካስተር ውል አንብቦ ወደደውና ለቅኝ አገሮቹ ሁሉ በማሳተሚያ ቤት አሰራጨው። በውሉ ውስጥ ኢሮኳውያን አለቆች ለእንግሊዞች እንዳሉ «ሰዎች ከመቀመጫችሁ ተርቀው ምን እንደሚያደርጉ ልታውቁ መታሠብ አትችሉም» ብለዋል። አስተርጓሚው ኮንራድ ቫይዘር (ታቸረዋገን) ተባለ።