የኩሎምብ ህግ

ከውክፔዲያ

የኩሎምብ ህግ ወይንም የኩሎምብ ግልብ ስኩየር ህግ በጠጣር ቻርጆች መካከከል ያለውን የጉልበት ዝምድና የሚያሳይ የፊዚክስ ህግ ነው። ለመጀመሪያ ጊዜ ተደርሶበት ሃሳቡ የታተመው በ1778 ዓ.ም. በፈረንሳዩ ኦግስቲን ኩሎምብ ነበር።

መሰረታዊ ቀመር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የስኬላር ቀመር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የኩሎምብ ህግ በስኬላር ወይንም በጨረር መልኩ ሊቀመጥ ይችላል። በስኬላር ሲጻፍ የጉልበት መጠንን ሲያሰላ፣ በጨረር ሲጻፍ የጉልበትን መጠንና አቅጣጫ ይሰጣል ማለት ነው። ህጉ በተሰጠው መልኩ የሚሰራው ነጥብ ቻርጅ ተደርገው ሊታሰቡ ለሚችሉ ሁለት ቻርጆች ነው። ወይንም በሌላ አነጋገር በሁለቱ ቻርጆች መካከል ያለው ርቀት ከሙላቶቹ ውስጣዊ ራዲየስ በሃይል ከፍ ለሚል ሙላቶች ነው።

በኩሎምብ ህግ ምሰረት፣ በቻርጅ (q1) እና (q2) ላይ በእያንዳንዳቸው በአንድ ጊዜ የሚያርፉት ጉልበቶች እንዲህ ይሰላሉ

r -- በሁለቱ መካከል ያለው ርቀት ሲሆን ke ደግሞ የውድር ቁጥር ነው። ፖዚቲቭ ጉልበት፣ መግፋትን ሲያመለክት፣ ነጌቲቭ ጉልበት መሳሳብን ያመለክታል:


የኩሎምብ ህግ መሰረታዊ ፀባይ። አንድ አይነት ሙላቶች ይጋፋሉ፣ የተለያዩ ቻርጆች ይሳሳባሉ።

ጨረራዊ ቀመር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ቦታ ላይ በተቀመጠች ሙላት ላይ ሌላው ሙላት q2መስኩ የሚያሳርፍባት ጉልበት መጠን እና አቅጣጫጨረር ቀመር ይሰላል። ከላይ የተሰጠው የኩሎምብ ህግ፣ መጠኑን ብቻ ነው ሚያሰላ።

የኩሎምብ ህግ ጨረራዊ ቀመር

- ከሙላት 2 በሙላት 1 ላይ የሚያርፍ ጉልበት፣
በሁለቱ ቻርጆች መካከል ያለው ርቀት ነው።
የጉልበቱን አቅጣጫ የሚያሳይ አሀድ ጨረር ነው። ከ ወደ [1] ለሚሰመር መስመር ትይዩ ነው።


ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ (እንግሊዝኛ) Coulomb's law, University of Texas


ተጨማሪ ንባብ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]