ደጃዝማች በየነ መርዕድ የባሌ አገረ ገዥና የልዕልት ሮማነወርቅ ባለቤት ነበሩ። ጣልያ ኢትዮጵያን በወረረው ጊዜ ከ1928 ዓ.ም. ጀምሮ ታዋቂ አርበኛ ሲሆኑ በ1929 ዓ.ም. ተይዘው ተገደሉ። የደጃዝማች መርዕድ በየነና የደጃዝማች ሶምሶን በየነ አባት ነበሩ።