ኢትዮጵያ

ከውክፔዲያ


የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ

የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የኢትዮጵያ አርማ
ሰንደቅ ዓላማ አርማ
ብሔራዊ መዝሙር ወደፊት ገስግሺ፣ውድ እናት ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያመገኛ
የኢትዮጵያመገኛ
ኢትዮጵያ በቀይ ቀለም
ዋና ከተማ አዲስ አበባ
ብሔራዊ ቋንቋዎች አማርኛ ሌሎች ቋንቋዎች ክልላዊ ዕውቅና አላቸው
መንግሥት
ፕሬዝዳንት
ጠቅላይ ሚኒስትር
ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ
ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ
ዶ/ር አብይ አህመድ
የመሬት ስፋት
አጠቃላይ (ካሬ ኪ.ሜ.)
ውሀ (%)
 
1,104,300 (26ኛ)

0.7
የሕዝብ ብዛት
የ፳፻ ዓ.ም. ግምት
የ፲፱፻፺፱ ዓ.ም. ቆጠራ
 
93,578,567 (13ኛ)

96,787,564
ገንዘብ ብር (ETB)
ሰዓት ክልል UTC +3
የስልክ መግቢያ 251
ከፍተኛ ደረጃ ከባቢ .et

ኢትዮጵያ ወይም በይፋ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢ.ፌ.ዲ.ሪ.)አፍሪካ ቀንድ የምትገኝ የረጅም ዘመን ታሪክ ያላት ሀገር ናት። በአፍሪካ ነፃነቷን ጠብቃ የኖረች ብቸኛ ሀገር ነች። በህዝብ ብዛት ከአፍሪካ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ስትሆን ፣ በቆዳ ስፋት ደግሞ አስረኛ ናት። ዋና ከተማአዲስ አበባ ናት።

አብዛኛዎቹ የአፍሪካ ሀገሮች ዕድሜያቸው ከአንድ ምዕተ-ዓመት የሚያንስ ሲሆን ፣ ኢትዮጵያ ግን ከጥንት ጊዜ ጀምሮ በንጉሠ-ነገሥታት እና ንግሥተ-ነግሥታት የተመራች ሀገር ናት። የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥት የአመጣጡን ዘር እስከ አስረኛው ዓመተ-ዓለም ድረስ ይቆጥራል። ኢትዮጵያ የሰው ልጅ ከጥንት ጊዜ ጀምሮ የኖረባት ቦታ እንደሆነች ብዙ የሳይንሳዊ መረጃ ተግኝቷል። በበርሊን ጉባኤ በኩል የአውሮፓ ሀያላት ሀገሮች አፍሪካን ሲከፋፍሏት፣ ኢትዮጵያ ነፃነቷን ጠብቃለች። የሊግ ኦፍ ኔሽንስ (League of Nations) አባል ከነበሩት ሶስት የአፍሪካ ሀገሮች አንዷ ነበረች። ከአጭር የኢጣልያ ወረራ ጊዜ በኋላም ከየተባበሩት መንግሥታት መሥራቾች አንዷ ናት። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት ነፃነታቸውን ሲያገኙ፣ ሰንደቅ-አላማቸውን በኢትዮጵያ ቀለሞች ማለትም በአረንጓዴቢጫ እና ቀይ ላይ ነው የመሠረቱት። አዲስ አበባ ደግሞ ለየተለያዩ በአፍሪካ ላይ ላተኮሩ አለም አቀፍ ድርጅቶች መቀመጫ ሆነች።

የዛሬዋ ኢትዮጵያ የትልቅ የግዛት ለውጥ ውጤት ናት። ከሰሜን ግዛቱዋ በጣም የተቀነሰ ሲሆን በደቡብ በኩል ደግሞ ተስፋፍቷል። በ ፲፱፻፷፯ (1967) ዓ.ም.፣ ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ከሥልጣን ሲወርዱ፣ የእርስ በርስ ጦርነት በሀገሩ ተባባሰ። ከዚህ ጊዜ በኋላ ኢትዮጵያ በተለያዩ የመንግሥት አይነቶች ተዳድራለች። ዛሬ አዲስ አበባ የአፍሪካ ሕብረት (African Union) እና የተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚክ ኮሚሽን ለአፍሪካ መቀመጫ ናት። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ከአፍሪካ ኃያል ሠራዊቶች አንዱ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪቃ የእራሷ ጥንታዊ ፊደል ያላት ሀገርም ናት።

ኢትዮጵያ ተፈጥሮ ያደላት ሀገር ናት። ከአፍሪካ ትላልቅ ተራራዎች እንዲሁም ከዓለም ከባህር ጠለል በታች በጣም ጥልቅ ከሆኑ ቦታዎች አንዳንዶቹ ይገኙባታል። ሶፍ ዑመር ከአፍሪካ ዋሻዎች ትልቁ ሲሆን ፣ ዳሎል ከዓለም በጣም ሙቅ ቦታዎች አንዱ ነው። ወደ ሰማንኒያ የሚቆጠሩ ብሔሮችና ብሔረሰቦች ዛሬ በኢትዮጵያ ይገኛሉ። ከእነዚህም ኦሮሞአምሀራ በብዛት ትልቆቹ ናቸው። ኢትዮጵያ በኣክሱም ሓውልት፣ ከአንድ ድንጋይ ተፈልፍለው በተሰሩ ቤተ-ክርስትያኖቹዋ እና በኦሎምፒክወርቅ ሜዳልያ አሸናፊ አትሌቶቹዋ ትታወቃለች። የቡና ፍሬ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በኢትዮጵያ ሲሆን ሀገሪቱዋ በቡናና ማር አምራችነት በአፍሪካ ቅድሚያ ይዛለች።

ኢትዮጵያ ከዓለም ሶስቱ ትላልቅ የአብርሃም ሀይማኖቶች ጋር ታሪካዊ ግንኙነት አላት። ክርስትናን በአራተኛው ምዕተ-ዓመት ተቀብላለች። ከሕዝቡ አንድ ሁለተኛው ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና ነው። የመጀመሪያው የእስላም ሂጅራ ወደ ኢትዮጵያ ነው የተከናወነው። ነጋሽ በአፍሪካ የመጀመሪያው የእስላም መቀመጫ ናት። እስከ ፲፱፻፸ ዎቹ ድረስ ብዙ ቤተ-እስራኤሎች በኢትዮጵያ ይኖሩ ነበር። የራስ ተፈሪ እንቅስቃሴ ኢትዮጵያን በትልቅ ክብር ነው የሚያያት።

ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ከስልጣን ከወረዱ በኋላ ድህነት በኢትዮጵያ በጣም ተስፋፍቶ ነበር። ሰማኒያ አምስት ከመቶ በላይ የሚሆነው የአባይ ወንዝ ውሀ ከሀገሩ የሚመጣ ቢሆንም በ ፲፱፻፸ ዎቹ በተከሰቱ ድርቆች በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ሞተዋል። ያንን ካሳለፈች በኋላ ሀገሪቱዋ አዲስ መንገድ በመፈለግ ላይ ትገኛለች።

“ኢትዮጵያ” የሚለው ቃል ትርጉሙንና አመጣጡን ለመመርመር በ፲፱፻፹፩ (1987 እ.ኤ.አ.) በወጣው ሰምና ወርቅ በተባለው የምርምር መጽሔት ፪ኛ ዓመት፣ ቁጥር ፬ አጥር ያለ ጽሑፍ አቅርበን፣ አንዳንድ ምሁራን፤ “ኢትዮጵያ ማለት ከግሪክ ቋንቋ የመጣ ቃል፣ ‘ፊቱ በፀሓይ የተቃጠለ፣ የተጠበሰ፣ ያረረ’ ማለት ነው ...” የሚሉት ትክክል እንዳልሆነ ለማሳየት፤ ናይጀርያ የሚባል አገርና፣ (Nigeria) ኒጀር (Niger) የሚባሉ አገርና ወንዝ በአፍሪካ እንዳሉ ጠቅሰን፣ ኔግራ፣ ኔግሮ፣ ኒገር፣ ኔግሪትዩድ (Negra, Negro, Nigger, Negritude) ለሚሏቸው ቃላት ወደ ላቲን/እንግሊዝኛ ቋንቋ ለመግባት ምክንያት ሆኑ እንጂ፣ ከላቲን ቋንቋ ተወስዶ ለአፍሪካ አገሮችና ወንዝ የተሰጠ ስም አይደለም በማለት፣ ኢትዮጵያ የሚለውም ቃል እንዲሁ ጥንታዊ ምንጩ ከግሪክ ሳይሆን ከአገራችን የወጣ ቃል መሆኑን ለመግለጽ ሞክረን ነበር።

አንድ-አንድ ቃላትን ስንመረምር በውስጣቸው የተደበቅ ምስጢር እናገኛለን። የተደበቀውን ምስጠር ለማግኘት ጥልቅ የታሪክና የቃላት ምርምርና ጥናት (Philology / Etimology) ማድረግ ያስፈልጋል። በብዙ ምርምርና ጥናትም ምስጢሩ የሚገለጥበት ጊዜ አለ። ለምሳሌ በግዕዝ፣ በትግርኛና፣ አማርኛ ‘አነ’፣ ‘እኔ’ የሚሉ ቃላት ስናገኝ፣ በላቲን/በእንግሊዝኛ ደግሞ ‘አይ’ (I - እንግሊዝኛ)፣ ‘ኢዮ’ (Io -ጣልያንኛ) አሏቸው። በግዕዝ፣ ትግርኛና፣ አማርኛ ‘ዓይን’ ‘ዓይኒ’ ለሚሉ ቃላት ደግሞ፣ በእንግሊዝኛ አይ (eye) እናገኛለን። በአማርኛና ትግርኛ፤ ‘ያለቀለት ጉዳይ’ ለማለት ‘ሙት፣ የሞተ ነገር’፣ ስንል በእንግሊዝኛ ‘ሙት ኢሹ’ (moot issue) ይላሉ። በግዕዝና፣ ትግርኛ፣ ‘መርዓ’ ስንል፣ በእንግሊዝኛ (marriage) ‘መረጅ’ ይላሉ። ፈርኦን (Pharaoh) ከሚባል ጥንታዊ የግብፅ ንጉሥም ወደ ግዕዝ፣ ትግርኛና አማርኛ፣ እንዲሁም ወደ እንግሊዝኛ ቃላት፤ ‘ፈሪሃ’ ‘ፍርሓት’ ‘fear’ (ፊር) ለሚሏቸው ቃላት ምንጭ የሆነ ይመስላል። ንጉሡ ታላቅና የሚፈራ የነበረ ነው የሚመስል። እነዚህን ለምሳሌ አቀረብን እንጂ እንደዚህ ብዙ የቃላት መቀራረብ እናገኛለን። “ማን ከማን ወሰደ? ታሪካዊ አመጣጡና አወራረዱስ እንዴት ነው?” የሚሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ነው የቃላት ጥናትና ምርምር የሚያስፈልግ።

አንድ-አንድ ቃላትም ከቋንቋችን ፈልቀው ይወጡና ዓለምን ዞረው ተመልሰው ሲመጡ ብርቅ አድርገን እንቀበላቸዋለን። ለምሳሌ በኃይለሥላሴ ዘመን ያኔ ልዕልት ፀሓይ ሲባል ከነበረው ሆስፒታል ጎን አዲስ የሕንፃ ኮሌጅ ተከፍቶ፣ ‘የመሃንድስ ኮሌጅ’ በመባል ይታወቅ ነበር። መሃንድስ ማለት ምን ማለት ነው? መሃንድስ ማለት መሃናስ/መሃንዳሰ ከሚል የዓረብኛ ቃል የመጣ ሲሆን፣ እርሱ ደግሞ ሃነፀ፣ ይሃንፅ፣ ማነፅ፣ ማሕፀን (ሕፃን የሚታነፅበት ቦታ) ... ወዘተ ከሚሉ የግዕዝ፣ የትግርኛና፣ የአማርኛም ቃላት ይዛመዳል። እንግዲያውስ ማነፅ ከሚለው ቃል መሃንዳስ ሆኖ ተጣመመና፣ ከዚያም መሃንድስ ተብሎ፣ ዞሮ ተመልሶ ብርቅ ቃል ሆኖብን ለሕንፃ ኮሌጀ መጠሪያ ሆነ። አሁንም ቢሆን ኢንጂኔር ለማለት መሃንድስ ሲባል እንሰማለን።

ሌላም ቃል ፋጡማ/ፋጢማ የሚል ስም ስንመለከት፣ ከነብዩ ሙሓመድ ሴት ልጆች ለአንዷ የተሰጠ መጠሪያ ነበረ። በዓረብኛ አባባል ግን ጠ/ጸ የሚለው ሳይሆን ተ የሚለው ፊዴል ድምፅ ነው። ይህም ማለት፣ ቃሉ “ፈቲማ” ብለው ሲሉ፣ ትርጉሙም፡ ፍጽምት፣ (Perfect) ማለት ነው። ስለዚህ ፈቲማ ማለት፣ ፈጺማ (ትግረኛ) ፈጸመች (አማርኛ) ማለት ነው።

ከሃያ አምስት ዓመታት በፊት ሰምና ወርቅ በተባለው የምርምር መጽሔት (1987 እ.ኤ.አ.) ያቀረብነው፣ “ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ትርጉሙ ምን ማለት ነው? ኢትዮጲስ የሚባለው ንጉሥስ ለምን ይህ ስም ተሰጠው ... ብለን በጠየቅንበት ጊዜ አጥጋቢ መልስ ባለማግኘታችን ቋንቋ ለሚመረምሩ (linguists) እንዲያተኩሩበት በዚሁ እንተወዋለን” በማለት ምርምሩን ደመደምነው።በዚህም ይህን መልስ አግኝተናል ኢትዮጲስ በመጽሐፈ አክሱም ዘንድ ኑቢያን የመሠረተው የካም ልጅ ኩሽ ልጅ ነበር። በዚህ መሠረት በኢትዮጵያ የሚኖሩት ኩሺቲክ ብሔሮች አባት በመሆኑ አገሩ 'ኢትዮጵያ' መባሉ እንደሚገባው ይታመናል።


በተክለ ጻድቅ መኩሪያ የተጻፈው “የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ኑብያ፣ (ናፓታ-መርዌ)” በተባለው መጽሐፍ በገጽ19-22 የካም ወገን የሆኑ 22 ነገሥታ

  1. ን ስምጠቅሶ፣ 55 ዓመት ከገዛው ከአክናሁስ ወይም ሳባ ፪ኛ (1985-1930 BC) ከክርስቶስ ልደት በፊት አንስቶ የ29 ነገሥታትን ስም አስቅምጦ፤ “... ራማ የተባለ የህንድ ንጉሥ ወደ ኢትዮጵያ ዘምቶ ማሸነፉንና ሕዝቡን እንደ ባርያ ...” ይገዛው እንደ ጀመረ ያትታል። ከዚያ ግን ሦስት የዮቅጣን ልጆች ተባብረው ተነስተው እሸነፉት፥ ገድለውም፣ አግዓዝያን (ነፃ አውጭዎች) ተብለው መንግሥቱን እንደ ያዙ ገልጾ፣ ከዚያ ቀጥለው የነገሡትን የ52 የኢትዮጵያ ነገሥታት ስም ይዘረዝራል። ከፊተኞቹ 29 ነገሥታትም የመጀመሪያዎቹ 10 ነገሥታት የሚከተሉት ናቸው:-

The meaning of the name Ethiopia

ከዚህም ዓምድ እንደሚታየው ኢትዮጲስ ፩ኛ ከ1856-1800 ከክርስቶስ ልደት በፊት፣ ለ56 ዓመት መንገሡ፣ ኢትዮጲስ ፪ኛው ደግሞ ከ1730-1700 ከክርስቶስ ልደት በፊት፣ ለ30 ዓመት ያህል መንገሡ በታሪክ ተጽፏል። ይህንን ያላነበቡ ምሁራኖቻችን ግን ኢትዮጵያ ማለት ከግሪክ ቋንቋ የመጣ ቃል፤ ‘ፊቱ በፀሓይ የተቃጠለ፣ የተጠበሰ፣ ያረረ ማለት ነው’ ይሉናል።

ታላቁ የግሪክ ተራኪና ባለ ቅኔ፣ ሆመር የኖረው 800 - 700 ከክርስቶስ ልደት በፊት ሲሆን፣ የግሪክ ስልጣኔ ዘመን ወይም የሄሌኒስቲክ ኤጅ (Hellenistic Age) ተብሎ የሚታወቀውም ከታላቁ እስክንድር ዘመን አንስቶ፣ ማለትም 300-30 ከክርስቶስ ልደት በፊት ድረስ ያለው ጊዜ ነው። ይህ ማለት ኢትዮጲስ ፩ኛ ከባለቅኔው ከሆመር በፊት አንድ ሺሕ ዓመት ቀድሞ የነገሠ ንጉሥ ነው።

እንግዲያውስ ምሁራኖቻችን ኢትዮጵያ ማለት ከግሪክ ቋንቋ የመጣ፤ ‘ፊቱ በፀሓይ የተቃጠለ፣ የተጠበሰ፣ ያረረ ማለት ነው’ ሲሉን፣ ሊመልሷችው የማይችሉ ሁለት ጥያቄዎች አሉን፣

1 - የጥንት የአገራችን ነገሥታት የግሪክን ቋንቋ ከሆመር መወለድ በፊት አንድ ሺሕ ዓመት አስቀድመው እንደምን ዐወቁት? ዘመኑ አቴናውያንና ስፓርታውያን የእርስ-በርስ ጦርነት (peloponnesian war 431-404 ከክርስቶስ ልደት በፊት) አንድ ሺሕ አራት መቶ ዓመት በፊት ነው። የግሪክ ቋንቋም በአካባቢው ከነበሩ መቄዶንያ፣ ማግያር፣ አናጦልያ ... ወዘተ ከመሳሰሉት ቋንቋዎች በምኑም ተለይቶ የሚታወቅ፣ ወይም የገነነ ልሳን አልነበረም። ስለዚህ እንዴት ተብሎ ይህንን ስም የአገራችን ነገሥታት ከግሪክ ቋንቋ ወሰዱት ማለት ይቻላል?

2 - ቋንቋውን ቢያውቁና ቃሉን ከግሪክ ወሰዱት ብንልም፣ እንዴት የአገራችን ነገሥታት ራሳቸውን፤ “ፊታችን በፀሓይ ያረረ፣ የተጠበሰ፣ የተቃጠለ ነውና ራሳችንን ኢትዮጲስ፤ ‘ፊታቸው በፀሓይ ያረረ፣ የተጠበሰ፣ የተቃጠለ’ ብለን እንጥራ ...” ብለው የራሳቸውን የንግሥ ስም አወጡ? ይህ ዓይነቱ አባባል ይታመናል? ፈጽሞ የማይመስል ወሬ ነው።

ምሁራኖቻችን እነዚህን ሁለት ጥያቄዎች ሲጠየቁ፣ “አፋፍ-ላፋፍ ስትሄድ አግኝቸ ሚዳቋ፣ በጅራቷ ብይዛት ዓይኗ ፍጥጥ አለ ...” እንደሚሉት ዓይናቸውን ከማፍጠጠና ከመቅበዝበዝ በቀር ሌላ የሚያድርጉት ሆነ የሚሰጡት ምንም መልስ የላቸውም።

በግሪክ ቋንቋ Αιθιοπία (አይትዮፕያ) ማለት ፊቱ በፀሓይ የተቃጠለ፣ የተጠበሰ፣ ያረረ ማለት ለመሆኑ አያጠያይቅም። ጥያቄው፤ የትኛው ቃል ከየትኛው መጣ? ነው። ግሪኮች የአገራችን ጥቁር ሰው አይተው ነው ቃሉን ወደ ቋንቋቸው ያስገቡት፣ ወይስ የአገራችን ነገሥታት ናቸው ስማቸውን ከግሪክ ቋንቋ ወስደው ለራሳቸው መጠሪያ ያደረጉት? ጥያቄው ይህ ነው!

የዚህ ዓይነቱ የተዛባ አስተሳሰብ የተላበሰ አንድ የሃይማኖት መሪ፤ “... ድንቅና ተአምር የሆነ የእግዚአብሔር ጥበብ የሚገርም ነገር አለ፣ ዓይናችን፣ አፍንጫችንና፣ ጆሮአችን እንዴት ብሎ ለመነጽር እንደሚገጥም ሆኖ መፈጠሩ ዕጹብ አይደለም?” እያለ ሰብኳል ይባላል። ይህ ግን የትኛው ቀዳሚ፣ የትኛው ኋለኛ መሆኑን ባለማወቁ ነው። መነጽር ነው ለዓይን፣ ለአፍንጫና ለጆሮ እንዲገጥም ሆኖ የተሠራ እንጂ፣ ፊታችን ለመነጽር እንዲገጥም ሆኖ አልተፈጠረም። ጥልቀት የሌለው ዐውቃለሁ ባይነት ግን ለእንዲህ ዓይነቱ መዘላበድ ያጋልጣል።

፪ኛ የቃላትና የፊዴላት ምርምር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

‘ፐ’ ‘ጰ’ ‘ጠ’ ‘ተ’

በመጀመሪያ (Αιθιοπία) ‘አይትዮፕያ’‘ኢትዮጵያ’ የሚሉ ቃላት ለመሆኑ የአገራችን ቃላት ናቸው ወይ ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው። ለመሆኑ ከግዕዝ፣ ከአማርኛና፣ ከትግርኛ ቋንቋዎች “ጰ” ወይም “ፐ” የሚል ፊዴል ያላቸውን ቃላት ብንፈልግ ምን እናገኛለን?

በግዕዝፅ በትግርኛና በአማርኛ ፖሊስ ከሚል ቃል ሌላ ‘ፐ’ ፊዴል ያለበት ምን ቃል አለ? ምንም ያለ አይመስለንም። የአገራችን ሰውም ፓሊስ ከማለት ‘ቦሊስ’ ማለት ነው የሚቀናው፥ ኢትዮጵያ ከማለትም ይጦብያ ማለት ይቀልለዋል። ‘ፐ’ እና ‘ጰ’ የሚባሉ ፊዴላትም ወደ አገራችን የፊዴል ሰነድ የገቡት በቅርብ ጊዜ ከመሆኑም በላይ፥ የውጭ ቃላትን ለመጻፍ እንዲያመቹ ተብሎ መሆኑ ግልጽ ነው። በፊደላት ሰንጠረጅም ከሁሉ በታች፣ ወይም ከመጨረሻ ቦታ መስፈራቸው ኋላ የመጡ ለመሆናቸው ተጨማሪ ማስረጃ ነው።

Trapezium‘ጰ’ የሚል ፊዴል ያላቸውን ቃላት የአገራችን ቋንቋዎች ብንፈልግም፤ ጴጥሮስ፣ ጳውሎስ፣ ቆጵሮስ፣ ጠረጴዛ ወዘተ... እናገኛለን። ይሁንና እነዚህ ሁሉ የውጭ ቃላት፣ ከመካከለኛው ምስራቅና ከኤውሮጳ የገቡ እንጂ የአገራችን ቃላት አይደሉም። ‘ጠረጴዛ’ የሚል ቃልም ትራፔዞይድ (trapezoid: a rectangular shaped object) ከሚለው የላቲን/የእንግሊዝኛ ቋንቋ የተገኘ እንጂ በመሰረቱ የአማርኛ ቃል አይደለም። በጥንታዊ ግዕዝ ጽሑፍም ስንመለከት፤ ‘ክሊዎፓትራ፣ የፕቶሎሚ ልጅ’ ለማለት፤ “አከልኡበጥራ፣ ወለተ በጥሊሞስ” ይላታል። ይህ የሚያሳየው “ፐ” የሚባል ፊዴል በጥንታዊ የአገራችን ቋንቋዎች ፈጽሞ እንዳልነበረ ነው። ክሊዎፓትራና አባቷ ፕቶሎሚ ግን ዘራቸው ግሪክ፣ ታላቁ እስክንድር ግብፅን አሸንፎ ከዚያው በኋላ ተክሏቸው የሄደ የግሪክ ገዢዎች ስለሆኑ፣ ስማቸው የግሪክ ስም ነው። ‘ፐ’ የሚል ፊዴልም አለበት።

ይህንን የፊዴላት ጥያቄ ያመጣነው ጥንታዊው የሁለቱ ነገሥታት ስም አጠራር ‘ኢትዮጲስ’ ወይም ‘ኢትዮፒስ’ ሊሆን እንደማይችል ለማስረዳት ነው። እንግዲያውስ ከዚህ የቃላት ምርምር የምናገኘው ነገር ካለ ይኽ ነው፤ በትክክለኛው ጥንታዊ አባባል ኢትዮጲስ፣ ኢይቶጲስ፣ ኢቶፒስ፣ አይቶፒስ... የሚሉ ስሞች ፈጽሞ የአገራችን ንገሥታት ስም ሊሆኑ እንደማይችሉ ነው።

ስለ ‘ጠ’ ፊዴል ካነሳን ደግሞ በግሪክ ቋንቋና በሌሎችም የኤውሮጳ ቋንቋዎች ‘ጠ’ የሚል ድምፅ የላቸውምና ‘ጠ’ የሚለውን በ ‘ተ’ እና ‘ፐ’ በሚሉ ፊዴላት ይተኳቸዋል። እንግዲያው ትክክለኛው አባባል ‘ይቶፒስ’ ሳይሆን “ይጦብስ” መሆን ይገባዋል እንላለን። ግሪኮች ‘ጠ’ ማለት ስላልቻሉ ነው (Αιθιοπία) ‘አይትዮፕያ’ ያሉት። እኛም ይኸው እስከ ዛሬ ኤውሮ‘ፓ’ ከማለት ኤውሮ‘ጳ’ እንደሚቀናን ማለት ነው።

የውጭ ታሪክ ጸሓፊዎች እነ ዮሴፍ ሃለቪ (Josph Halevi)፣ እኖ ሊትማን (Enno Litman)፣ ኤድዋርድ ግላሴር (Edward Glaser)፣ ኮንቲ ሮሲኒ (Conti Rossini)፣ ጂ. ሪክማንስ (G. Rickmans) የመሳሰሉትና ሌሎችም የውጭ አገር ሰዎች ያቀረቡት ጽሑፍ ይጦብያ ለማለት ስላልቻሉ ይቶፕያ፣ ኢቶፕያ፣ ሆኖ ወደ ቋንቋችን ሲተረጐም ‘ኢትዮጵያ’ ተብሎ ሊጸና ቻለ እንጂ ይህ ስም ትክክለኛ የአገራችን ይሁን የንጉሦቻችን ስም እንዳልሆነ ግልጽ ነው።

በአገራችን ታሪክ የምናገኘው ሓቅ ደግሞ፣ “ይጦብያ”፣ “ይጦብስ” የሚል ስም ለሕዝብና ለአገር ቀርቶ ለተራ ንጉሥም የማይሰጥ እንደ ነበረ ነው። ሕዝቡ ነገደ አግዓዝያን፣ አገሩ ብሔረ አግዓዚ፣ ቋንቋው ልሳነ ግዕዝ ነበር። ነገሥታቱም በየክፍለ-ሃገሩ ስም፤ የትግራይ ንጉሥ፣ የወሎ ንጉሥ፣ የጎጃም ንጉሥ፣ የሸዋ ንጉሥ... ወዘተ፣ ይባሉ ነበር። “ይጦብያ” ተብሎ የሚታወቀው ሁሉን የጠቀለለ ንጉሠ-ነገሥቱ ብቻ ነበር። ይህም የጥንቱን የይጦብስ ንጉሥን ጠቅላይ ስም ወራሽነት መያዙ ለማሳየት ሆን ብሎ የተደረገ ብልሓት ይመስላል።

ይጦብስ ማለትስ ምን ማለት ነው? በግዕዝ በትግርኛና በአማርኛም “መጥበስ” የሚል ቃል አለ። ቃሉም ሲራባ፤ ጠበሰ፣ ተጠበሰ፣ ይጠብስ፣ ትጠብስ፣ ጥቡስ፣... ወዘተ፣ እያለ ይራባል። እንግዲያውስ ይጦብስ ማለት ጥንታዊ ትርጉሙ፤ ይጠብሳል፣ ያቃጥላል፣ ኃይለኛ ንጉሥ ነው! ተብሎ ጠላቶችን ለማስፈራሪያ የወጣ ስም ይመስላል እንጂ ከግሪክ ቋንቋ ተወስዶ ለአገራችን ነገሥታት ‘ፊቱ የተጠበሰ፣ በፀሓይ የተቃጠለ’ ተብሎ የተሰጠ ስም ነው ማለት አይቻልም።

ይህንን የምንለው ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ከግሪኮች የመጣ ነው ለሚሉት አጉል ምሁራን ስሕተታቸውን ለማሳየት ነው እንጂ፣ በየዘመናቱ ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ልዩ-ልዩ ትርጉሞች እንደ ተሰጡት አይጠረጠርም። ለምሳሌ ኢትዮጵያ ማለት መልካም መዓዛ ያለው ዕጣን ነው የሚሉ አሉ። የለም፣ ታላቅና ጠቅላይ ማለት ነው የሚሉም አሉ። ከዘመናት ብዛትልዩ-ልዩ ትርጉሞች እንደተሰጡት አያጠራጥርም። የሚደንቀው ነገር ግን መሃነስ/መሃንደስ የሚል ቃል ዓለምን ዞሮ ወደኛ መሃንድስ ሆኖ ሲመለስ ህንፃ የሚለውን ትርጉሙን እንዳልሳተ፣ ‘ይጦብስ’ የሚለውም ቃል እንዲሁ የቃሉ አባባል ትንሽ ተወላግዶ በግሪኮች አነጋገር ‘ይቶፒስ’ ቢባልም የመቃጠልና የመጠበስ ትርጉሙን ሳይስት እንደ ተቀመጠ ለብዙ ዘመናት የቆየ ይመስላል።

እዚህ ላይ ‘ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ?’ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው። ምናልባት በይጦብስ ዘመን የአገራችን ተጓዦች ወይም ነጋዴዎች ከግሪክ ሰዎች ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ሲገናኙ፤

“እናንተ እነማንናችሁ?”ብለዋቸው ይሆናል። “የይጦብስ ሰዎች ነን”፣ብለው መልሰዋል። “ይጦብስ ማለትስ ምን ማለት ነው?” ብለው ሳይጠይቋቸው አልቀሩም። “የሚያሳርር፣ የሚያቃጥል፣ የሚጠብስ ኃይለኛ!” ማለት ነው ብለው አስረድተዋቸዋል።

ከዚያ ወድያ ግሪኮችጠቆር ያለውን ሰው ባዩ ቁጥር (Αιθιοπίs) “ይጦብስ” እያሉ መጥራት ጀምረው፣ ቃሉም ወደ ቋንቋቸው ከመግባቱም በላይ፣ “ይጠብስ” የሚለውን ጥንታዊውን ትርጉም ሳይስት ለጥቁር አፍሪካዊ ሁሉ ‘ፊቱ የተጠበሰ፣ በፀሓይ የተቃጠለ’ (Αιθιοπία) ‘ኢትዮጵያ’ የሚል መጠሪያ ለመሆን የበቃ ነው የሚመስል።

ምርምራችን በዚህ ያበቃል።[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ምንጭ፡ https://ethiopiazare.com/amharic/history/history/4204-the-meaning-of-the-name-ethiopia-by-ge-gorfu Archived ጃንዩዌሪ 17, 2021 at the Wayback Machine

ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ቅድመ ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ የሰው ልጅ ከነበረባችው ቦታዎች አንዷ መሆኗ ትታወቃለች። የሰው ፍልሰት ጥናቶች ፣ የቅሪተ አካል ጥናቶችና ሌሎች የሳይንሳዊ ዘዴዎች ይህን ያረጋግጣሉ። ድንቅነሽ የምትባለው በአፋር ክልል ውስጥ የተገኘችው አጽም በአለም በዕድሜ ሁለተኛ ጥንታዊ ናት። ከ 3.2 ሚሊዮን ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ እንደኖረች ይገመታል። ሌሎችም ታዋቂ አጽሞች በኢትዮጵያ ተገኝተዋል። ከዚህም በተጨማሪ ኢትዮጵያ የክርስትና እምነት ደሴት በመሆን የቆየች ታላቅ ሀገር ናት።

የመጀመሪያዎቹ መንግስታት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር።

የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ።

ከአውሮፓ ጋር የታደሰ ግንኙነት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የንጉሠ ነገሥት ፋሲለደስ ቤተ-መንግሥት

በ ፲ ፭ኛው ምዕተ-ዓመት መጀመሪያ ኢትዮጵያ ከአክሱም ጊዜ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአውሮፓ ጋር ግንኙነት ጀመረች። ከእንግሊዝ ንጉሥ ሄነሪ አራተኛ (Henry IV) ወደ የአቢሲኒያ ንጉሠ-ነገሥት የተላከ ደብዳቤ እስከ ዛሬ ድረስ አለ። በ1428 እ.ኤ.አ. አፄ ይስሐቅ ወደ የአራጎን ንጉሥ አልፎንዞ አምስተኛ (Alfonso V) ሁለት መልክተኞች ልከው ነበር። ግን የመጀመራያው ያልተቋረጠ ግንኙነት በአፄ ልብነ ድንግል ስር ከፖርቱጋል ጋር ከ1508 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ነው የተካሄደው።

ኢትዮጵያ በአህመድ ግራኝ ስትጠቃ ፣ ፖርቱጋል አራት መቶ ወታደሮችና የጦር መሳሪያ በመላክ ኢትዮጵያን ረድታለች። አፄ ሱስንዮስ በፖርቱጋልና እስፓንያ ተጽዕኖ እና ተጨማሪ እርዳታ ከመፈለጋቸው የተነሳ ወደ የሮማ ካቶሊክ ክርስትና ተለወጡ ፤ የኢትዮጵያ ይፋ ሀይማኖትንም አደረገቱት። ይህ ውሳኔ ወደ ግዙፍ ተቃውሞና ጦርነት አመራ። በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ከሞቱ በኋላ ፣ የአፄ ሱስንዮስ ልጅ አፄ ፋሲለደስ1632 እ.ኤ.አ. ኢትዮጵያ ወደ አርቶዶክስ ክርስትና መመለሷን አወጁ። አውሮፓውያኖቹንም ከኢትዮጵያ አስወጡ።

ዘመነ መሳፍንት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

አፄ ቴዎድሮስ በአንበሶች ተከበው

፲፯፻፶፭ (1755) እስከ ፲፰፻፶፭ (1855) እ. ኤ. አ. ኢትዮጵያ እንደገና ከአለም ጉዳዮች ተገላ ነበር። ይህ ጊዜ «ዘመነ-መሳፍንት» ይባላል ምክኒያቱም የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥቶች በራስ ሚካኬል ስሁል ፣ ራስ ወልደ ሥላሴ ፣ ራስ ጉግሳ እና በመሳሰሉት ቁጥጥር ስር ነበሩ። ራስ ጉግሳ በ፲፯ኛው ክፍለ ዘመን ጎንደርን በመምራታቸው የቤተ-መንግሥቱን ቋንቋ ከአማርኛ ወደ ኦሮምኛ ለውጠው ነበር።

የኢትዮጵያ ግለልኘነት ያበቃው ከእንግሊዝ ጋር ግንኙነት ስትጀምር ነው። ኢትዮጵያ እንደገና የተዋሀደችው እንዲሁም የዘውዱ ስልጣን የተጠናከረው በ ፲፰፻፶፭ (1855) እ. ኤ. አ. በአፄ ቴዎድሮስ ምክኒያት ነው። የሰሜን አሮሞዎችና ትግሬዎች አመፅና የግብፆች ተደጋጋሚ ድንበር መጣስ የአፄ ቴዎድሮስ ስልጣን እንዲዳከም አደረጉት። በመጨረሻም ከእንግሊዝ ጋር በነበረው ጦርነት እስረኛ አልሆንም ብለው አፄ ቴዎድሮስ እራሳቸውን አጠፉ። በ ፲፰፻፷፰ (1868) እ. ኤ. አ. ኢትዮጵያና ግብፅ ጉራ በሚባለው ቦታ ተዋጉ። በአፄ ዮሐንስ አራተኛ የተመሩት የሰሜን ኢትዮጵያ ኃይሎች ድል ተቀናጁ።

፲፰፻፹፱ (1889) እና በ ፲፰፻፺ (1890) ዎቹ እ.ኤ.አ. መጀመሪያ ፣ የሸዋ ንጉሥ ሳህለ ሥላሴ ከዚያም ዳግማዊ አፄምኒልክ በራስ ጎበና እርዳታ አማካኝነት ሀገሯን ወደ ደቡብና ምሥራቅ ማስፋፋት ጀመሩ። ከአህመድ ግራኝ ወረራ በኋላ በኢትዮጵያ ቁጥጥር ስር ያልነበሩ ፣ ሌሎች ደግሞ በማንኛው ጊዜ በኢትዮጵይ ቁጥጥር ስር ያልነበሩ ቦታዎች በዳግማዊ አፄ ምኒልክ አገዛዝ ጊዜ በኢትዮጵያ ስር ሆኑ። ከዚህ ጊዜ በኋላ የኢትዮጵያ ድንበር ብዙ አልተለወጠም። ከ ፲፰፻፹፰ (1888) እስከ ፲፰፻፺፪ (1892) እ. ኤ. አ. ድረስ የነበረው የሰፋ ድርቅ ከኢትዮጵያ ህዝብ በአንድ ሶስተኛ የሚገመተውን ቀጥፎአል።

የአውሮፓ ሽሚያ ለአፍሪካ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በ ፲፰፻፹ (1880) ዎቹ እ. ኤ. አ. የአውሮፓ መንግሥቶች በበርሊን ጉባኤ ተስማምተው አፍሪካን በቅኝ ገዢነት መከፋፈል ጀመሩ። በኢትዮጵያ እና ጣልያን መካከል የነበሩ የዚያ ዘመን ውዝግቦች ወደ አድዋ ጦርነት በ ፲፰፻፹፰ (1888) ዓ. ም. አመሩ። በጦርነቱ የጣልያን ትልቅ ዘመናዊ ጦር በኢትዮጵያ ጦር ትልቅ ሽንፈት የደረሰበት መሆኑ ዓለምን አስደነቀ።

የአድዋ ጦርነት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በአጼ ምኒልክ በተመራው የኢትዮጵያ ሠራዊትና ባህር አቋርጦ ከአውሮፓ ከመጣው የጣሊያን ሠራዊት ጋር የተካሄደው የዓድዋው ጦርነት በታሪክ ውስጥ ከሚጠቀሱ ጉልህ ክስተቶች መካከል አንዱ ነው።

የኢትዮጵያ አርበኞች የዓድዋ ድል ጣሊያን አፍረካ ውስጥ በተለይ ደግሞ በምሥራቁ የአህጉሪቱ አካባቢ ለማስፋፋት አቅዳ የተነሳችለትን የቅኝ ግዛት ዕቅድን ያጨናገፈ ከመሆኑ ባሻገር፤ በዘመኑ የአውሮፓዊያን ሠራዊት በአፍሪካዊያን ካበድ ሽንፈት ሲገጥመው የመጀመሪያ በመሆኑ ድንጋጤንም ፈጥሮ ነበር።

ለዓደዋው ጦርነት ዋነኛ ምክንያት የሆነው በኢትዮጵያና በጣሊያን መንግሥታት መካከል የተፈረመው የውጫሌ ውል ነበር። በዚህ ውል አንቀጽ 17 ላይ በጣሊያንኛ የሰፈረው ጽሑፍ ኢትዮጵያ ከአውሮፓ መንግሥታት ጋር ማድረግ የምትፈልገውን ግንኙነት በጣሊያ በኩል መሆን እንዳለበት ሲያመለክት የአማርኛው ግን ግንኙነቱን በኢጣሊያ በኩል ማድረግ ትችላለች ይላል።

  • የአድዋ ማዕከል የአዲስ አበባ እምብርት ላይ ሊሰራ ነው
  • ጣልያን በተሸነፈችበት አድዋ ቆንስላዋን ለምን ከፈተች?
  • መከፋፈል ያጠላበት ጉዞ አድዋ

ይህ የትርጉም ልዩነት እንደታወቀ መጀመሪያ ላይ አጼ ምኒልክ የውሉን አንቀጽ አስራ ሰባት እንደማይቀበሉ ካሳወቁ በኋላ ቀጥሎም የውጫሌውን ውል ሙሉውን ውድቅ አደረጉት። ይህም ጣሊያን ጦሯን በማዝመት ወረራ እንድትፈጽም ሊያደርጋት እንደሚችል የተረዱት ንጉሡ ዝግጅት ማድረግ ጀምረው ነበር።

የተፈራው አልቀረም የጣሊያን ሠራዊት ለወረራ እንቅስቃሴ ጀመረ። ከኢትዮጵያ በኩል የንጉሡን ጥሪ ተከትሎ ከመላዋ አገሪቱ የተሰባሰበው ሠራዊት አገሩን ከጣሊየን ወረራ ለመከላከል ያለውን መሳሪያ ይዞ ወደ ሰሜን አቀና።

በአጼ ምኒልክ የተመራው ሠራዊት እስከ ሃያ ሺህ የሚደርሱ ፈረሰኞችን ጨምሮ ከአንድ መቶ እስከ መቶ ሃያ ሺህ የሚገመት አርበኛ ወደ አድዋ ሲተም መነሻው ከአዲስ አበባ ነበር። ሠራዊቱ ዓድዋ ለመድረስ አንድ ሺህ ኪሎ ሜትር አካባቢ በእግሩና በጋማ ከብት መጓዝ ነበረበት።

ሠራዊቱ ዓድዋ ከደረሰ በኋላ ለፍልሚያ አመቺ ጊዜን ሲጠብቅ ቆይቶ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም ከ17 ሺህ በላይ ወታደሮችን ካሰለፈው አውሮፓዊ ኃይል ጋር ጦርነት ገጠመ።

ጦርነቱ በተጀመረ በግማሽ ቀን ውስጥ የኢትዮጵያ አርበኞች በሁሉም አቅጣጫ በጣሊያን ሠራዊት ላይ በሰነዘሩት ጥቃት ከባድ ጉዳት ስላደረሱበት በአንድ ላይ ተሰልፎ ኢትዮጵያዊያኑን ለመቋቋም ሳይችል ቀረ።

በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። በዚህም መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያም ተማርኳል። በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄኔራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄኔራል ባራቴሪ ሸሽቶ አመለጠ።

የግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ

በ ፳ኛው ምእት ሁለተኛው ሩብ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ኢትዮጵያን ከልጅ ኢያሱ በኋላ መምራት ጀመሩ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ለአፍሪካ ሕብረት መቋቋም ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።

የኢትዮጵያ ነጻነት በጣልያን ወረራ ከ ፲፱፻፴፮ (1936) እስከ ፲፱፻፵፩ (1941) እ. ኤ. አ. ድረስ ቢጠቃም በጀግኖችዋ መከታ ተጠብቋል። በአዚህ ጥቃት ጊዜ ዓፄ ኃይለሥላሴ በ ፲፱፻፴፭ (1935) እ. ኤ. አ. በሊግ ኦፍ ኔሽንስ (League of Nations) ፊት የሚታወስ ንግግር በአማርኛ አደረጉ። ይህ ንግግር በዓለም ታዋቂ አደረጋቸው። እንዲሁም በ ፲፱፻፴፭ (1935) እ.ኤ.አ. በ ታይም (Time) መጽሄት «የዓመቱ ሰው» አስባላቸው። ጣልያን ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ውስጥ መሳተፍ ስትጀምር ፣ እንግሊዝ ከኢትዮጵያዊ ተዋጊዎች ጋር ኢትዮጵያን ነጻ አወጣች። ግን እስከ ፲፱፻፵፫ (1943) እ. ኤ. አ. ድረስ አንዳንድ ጣልያኖች በደፈጣ ያለ ስኬት ይዋጉ ነበር። በ ፲፱፻፵፪ (1942) እ. ኤ. አ. ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ባርነት እንደ ተከለከለ አወጁ።

ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ጀግና ሆነው ቢታዩም ፣ የ ፲፱፻፸፫ (1973) እ.ኤ.አ. ዓለም አቀፍ የነዳጅ ቀውስ ፣ የምግብ ዕጥረትና የድንበር ጦርነቶች ተቃውሞ አስነሱ። ከዚያም በ ፲፱፻፸፬ (1974) እ. ኤ. አ. በሶቪየት ሕብረት የተደገፈውና በመንግስቱ ኃይለ ማርያም የተመራው ደርግ (ደርግ ማለት ኮሚቴ ማለት ነው) ዓፄ ኃይለ ሥላሴን ከስልጣን አስወረደ።

ኮምዩኒዝም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የተለያዩ መፈንቅለ መንግሥቶች ፣ የሰፋ ድርቀትና ስደተኞች የደርግ ሥርዓት ትልቅ ችግሮች ነበሩ። በ ፲፱፻፸፯ (1977) እ. ኤ. አ. ሶማሊያ ኦጋዴንን በመውረሯ የኦጋዴን ጦርነት ተነሳ። በሶቪየት ሕብረት ፣ ኩባደቡብ የመንምስራቅ ጀርመንሰሜን ኮሪያ የመሳሪያ እርዳታ እንዲሁም ወደ ፲፭ ሺህ በሚቆጠሩ የኩባ ወታደሮች ድጋፍ አማካኝነት ደርግ ኦጋዴንን እንደገና መቆጣጠር ቻለ።

በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች በቀይ ሽብር ፣ የግዴታ ስደት ፣ ወይም ረሀብ ሞተዋል። መንግስቱ ቀይ ሽብር ያካሄደው በተቀዋሚዎች በተፈጸመው ነጭ ሽብር መልስ እንደሆነ ጠቅሷል። በ ፳፻፮ (2006) እ. ኤ. አ. መንግስቱ ኃይለ ማርያም በሌሉበት የሞት ቅጣት ተፈርዶባቸዋል።

በ ፲፱፻፹ (1980) ዎቹ መጀመሪያ የተከሰቱ ድርቀቶች ምክኒያት ስምንት ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ሲራብ ፣ አንድ ሚሊዮን ደግሞ ሞተዋል። ተቃውሞ በትግራይና ኤርትራ ክልሎች ተስፋፋ። በ ፲፱፻፹፱ (1989) እ. ኤ. አ. ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ከሌሎች እንቅስቃሴዎች ጋር በመቀናጀት የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባርን መሠረተ። የሶቪየት ሕብረትም ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ መቀነስ ጀመረች። የኢኮኖሚ ችግሮች ተከሰቱ ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ተዳከመ።

በሜይ ፲፱፻፺፩ (1991) እ. ኤ. አ. የኢ. ህ. አ. ዴ. ግ. ጦር ወደ አዲስ አበባ አመራ። የመንግስት ኃይሎች ምንም አይነት የውጭ እርዳታ ስላላገኙ ፣ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ.ን ጥቃቶች መቋቋም አልቻሉም። መንግስቱ ኃይለ ማርያም ወደ ዚምባብዌ ሄደው እስከ ዛሬ ድረስ በዛችው ሀገር ይኖራሉ። ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ. ፹ ፯ አባላት ያሉት የሽግግር መንግሥት መሠረተ። በጁን ፲፱፻፺፪ (1992) እ. ኤ. አ. የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፣ እንዲሁም በማርች ፲፱፻፺፫ (1993) እ. ኤ. አ. የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኅብረት የሽግግር መንግሥቱን ለቀው ወጡ። በ ፲፱፻፺፬ (1994) እ. ኤ. አ. ሁለት የሕግ አውጪ ምክር ቤቶችንና የፍትሕ ስርዓትን የሚደነግግ አዲስ ሕገ መንግሥት ተፃፈ። የመጀመሪያው ምርጫ በሜይ ፲፱፻፺፭ (1995) እ.ኤ.አ. ተካሄደ። አቶ መለስ ዜናዊ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሁም ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ።

በቅርብ ጊዜ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በየተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ ኢትዮጵያና ኤርትራ በፌደሬሽን ተዋህደው ነበር። በ ፲፱፻፺፫ (1993) እ.ኤ.አ. በተካሄደውና የተባበሩት መንግሥታት በታዘበው ሕዝበ ድምፅ ፣

በወቅቱ ስልጣንን በጠመንጃ አፈሙዝ የያዙትና የኤርትራን መገንጠል በሚፈልጉት በህውአትና ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ አማካይነት ለኤርትራ ህዝብ ‹ባርነት› ወይንስ ‹ነፃነት› ተብሎ እንዲመርጡ ተገደው ማንም ባርነትን የሚመርጥ የለምና ነፃነትን መረጡ ተባሎ  በረሃ ገብተው ሲታገሉለት የነበረውን አላማ ስልጣናቸውን በመጠቀም አስፈፅመው ከ ፺፱ ከመቶ በላይ የሚሆነው የኤርትራ ሕዝብና በውጭ ሀገር የነበሩ ኤርትራውያን ከኢትዮጵያ መገንጠልን መርጠዋል። በሜይ ፳፬ ፣ ፲፱፻፺፫ (1993) እ. ኤ. አ. ኤርትራ ከኢትዮጵያ ነፃነቷን አወጀች።

በሜይ ፲፱፻፺፰ (1998) እ. ኤ. አ. የድንበር ውዝግብ እስከ ጁን ፳፻ (2000) እ. ኤ. አ. ወደ ቀጠለው የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት አምርቶአል። ይህ ጦርነት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚን ጎድቶአል። በሜይ ፲፭ ፣ ፳፻፭ (2005) እ.ኤ.አ. አጠቃላይ ምርጫ ቢካሄድም ተቃዋሚዎች ማጭበርበር እንደነበረ ወንጅለዋል። በአጠቃላይ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ከ ፪፻ (200) በላይ የፓርላማ መቀመጫዎችን አሸንፈዋል። ግን አንዳንድ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አባሎች ከምርጫው በኋላ ከነበረው ረብሻ ጋር በተያያዘ ታስረው ነበር። በአሁኑ ጊዜ ያለው የፖለቲካ ስርአት በብሄር ላይ የተመሰረተ ፌደራላዊ ስርአት ነው፡፡

መልክዓ-ምድር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኢትዮጵያ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ ከ 3-14 ዲግሪ ሰሜን እና ከ 33-48 ዲግሪ ምሥራቅ የምትገኝ አገር ስትሆን የቆዳ ስፋቱዋም 1,127,127 ካሬ ኪ.ሜ. ነው። በሰሜን ከኤርትራ ፣ በምዕራብ ከሱዳንደቡብ ሱዳን ፣ በደቡብ ከኬኒያ ፣ እንዲሁም በምሥራቅ ከጅቡቲ እና ከሶማሊያ ጋር ትዋሰናለች። የኢትዮጵያ አብዛኛው ግዛት በተራሮች እና አንባዎች የተሞላ ሲሆን ፣ ታላቁ የምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ እነዚህኑ ከፍተኛ ቦታዎች ከሰሜን ምሥራቅ ወደ ደቡብ ምዕራብ በመጋደም ለሁለት ይከፍላቸዋል። በስምጥ ሸለቆው ዙሪያም በረሃማ የሆኑ ዝቅተኛ ቦታዎች ይገኛሉ። ይሄን መሰሉ የመልክዓ-ምድር ልዩነት አገሪቷ የተለያዩ የአየር ንብረት ፣ የአፈር ፣ የዕፅዋት እና የሕዝብ አሰፋፈር ገጽታዎች እንዲኖሯት አስችሏታል። በከፍታና በመልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ የተነሣ በኢትዮጵያ ውስጥ ሦስት ዓይነት የአየር-፡ ንብረት ክልሎች ይገኛሉ። እነሱም፦

  • ደጋ – ከፍታቸው ከባሕር ጠለል 2400 ሜትር የሚጀምር እና የሙቀት መጠናቸው ከ 16 ዲግሪ ሴ. ግ. የማይበልጥ
  • ወይናደጋ – ከፍታቸው ከባሐር ጠለል ከ 1500 እስከ 2400 ሜትር ፣ ሙቀታቸውም ከ 16 ዲግሪ ሴ. ግ. እስከ 30 ዲግሪ ሴ. ግ. የሚደርስ ፣ እና
  • ቆላ – ከባህር ጠለል በታች ጀምሮ እስከ 1500 ሜትር ከፍታ ያላቸው ፣ የሙቀት መጠናቸውም ከ 30 ዲግሪ ሴ. ግ. እስከ 50 ዲግሪ ሴ. ግ. የሚደርስ አካባቢዎች ናቸው።

ዋናው የዝናብ ወቅት ከሰኔ አጋማሽ እስከ መስከረም አጋማሽ ሲሆን ፣ ከሱ ቀደም ብሎ አልፎ አልፎ የሚጥል የበልግ ዝናብ በየካቲት እና በመጋቢት ይከሰታል። የተቀሩት ወራት በአብዛኛው ደረቅ ናቸው።

አስተዳደራዊ ክልሎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]


፲፱፻፺፮ (1996) እ.ኤ.አ. በፊት ኢትዮጵያ በ ፲፬ ክልሎች ተከፍላ ነበር። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጽያ ውስጥ ፱ አስተዳደራዊ ክልሎች ይገኛሉ። አወቃቀራቸውም በህገ-መንግስቱ በተደነገገው መሰረት «በህዝብ አሰፋፈር ፤ ቋንቋ ማንነት እና ፈቃድ ላይ» ተመስርቶ ሲሆን ክልሎቹም፦

1. የትግራይ ክልል

2. የአፋር ክልል

3. የአማራ ክልል

4. የኦሮሚያ ክልል

5. የሶማሌ ክልል

6. የቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል

7. የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል

8. የጋምቤላ ሕዝቦች ክልል

9. የሐረሪ ሕዝብ ክልል

10. የሲዳማ ሕዝቦች ክልል

11. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል

ሲሆኑ በተጨማሪም

12. አዲስ አበባ እና

13. ድሬዳዋ እራሳቸውን የቻሉ የአስተዳደር አካባቢዎች ሆነው ተዋቅረዋል።

  • ዋና ሰሪ ምዕራፍ ሰሎሞን

አስተደዳራዊ ክልሎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ስዕል:Ethiopia Provinces numbered 300px.png
የኢትዮጲያ ክልሎች በቁጥር ተሰይመው
ክልል የሕዝብ ብዛት የመሬት ስፋት (ካሬ ኪ.ሜ.) ዋና ከተማ
1. ትግራይ (ክልል) 450,000 33,016 መቀሌ
2. አፋር(ክልል) 600,000 1,788 ሰመራ
3. አማራ(ክልል) 800,000 70,314 ባህር ዳር
4. ኦሮሞ(ክልል) 50,000,000 7,283


አዳማ
5. ሶማሌ(ክልል) 140,000 199,049 ጅጅጋ
6. ቤንሻንጉል-ጉምዝ(ክልል) 400,000 24,110 አሶሳ
7. ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች (ክልል)


600,000 55,660 አዋሳ
8. ጋምቤላ (ክልል) 200,000 87,342 ጋምቤላ
9. ሐረሪ

(ክልል)

1,000,000 34,270 ሀረር
10. ሲዳማ

(ክልል)

700,000 75,002 አዋሳ
11. አዲስ አበበ (ክልል) 3,000,000 2,257 አዲስ አበበ
12. ድሬድዋ (ክልል) 103,000 103,000 ድሬድዋ

ሕዝብ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የኢትዮጵያ ሕዘብ ቁጥር ከ ፼፼ (100000000) በላይ ሲሆን እንዲሁም ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4 በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ።

ቋንቋዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዋና መጣጥፍ፦ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ

በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ።

ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞሶማልኛአፋርኛሲዳምኛሃዲያኛቀቤንኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛኩናማኛጉሙዝኛሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። እንደ ወላይትኛ ፣ [[ጋሞኛ]፣ ጎፍኛ ፣ ከፋኛሃመርኛ የመሳሰሉት የኦሞአዊ ቋንቋ ዘሮች ሲሆኑ አማርኛ ፣ ትግርኛጉራጊኛስልጢኛሀደሪኛአርጎብኛ፣ ጎፍኛ እና መሰል ቋንቋዎች ከሴማዊ ቋንቋዎች ይመደባሉ። ዘጋቢ በአወል ሙሀመድ ደራ

ፊደል[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የሴሚቲክ ምንጭ ያላቸው እንደ ትግርኛና አማርኛ ያሉት ቋንቋዎች የራሱ የሆነ የተለየ የፊደል ስርአት ያላቸው ሲሆን ይህም ኢትዮጵያን ከአፍሪቃ ብቸኛዋ ባለ ጥንት ፊደል ሀገር ያደርጋታል። እነኚህ የሴሚቲክ ምንጭ ያላችው ቋንቋዎች ግዕዝ የተባለ በአሁኑ ወቅት ከቤተክርስትያን ውጭ ለዕለት ተዕለት ግልጋሎት ላይ የማይውል ግንድ ዘር አላቸው።

በኣሁኑ ጊዜ ግዕዝ በዩኒኮድ ዕውቅና ያገኙትን የቢለን፣ ቤንች፣ ምኢን፣ ሙርሲ፣ ሱሪ፣ ትግረ፣ ትግርኛ፣ ኣገው፣ ኣውንጂ፣ ኦሮሚፋ፣ ዓማርኛ፣ ዲዚ፣ ዳውሮ፣ ጉሙዝ፣ ጉራጌ፣ ጋሞ ጎፋ እና ግዕዝ ቋንቋዎች የሚጋሯቸውን ቀለሞችና ሌሎች ያጠቃልላል። በፊደሉ ከሚጠቀሙ ቋንቋዎች መካከል ሓረሪ ኣንዱ ነው። መጽሓፍ ቅዱስ ሙሉዉን ወይም በከፊል ከ፲፭፻፮ ዓ.ም. ጀምሮ በግዕዝ ቀለሞች በማተሚያ ቤቶች ከታተሙባቸው ቋንቋዎች መካከል ሃዲያ፣ ሲዳሞ፣ ከምባታ፣ ኦሮሞ፣ ወላይታ እና ጌዴኦ ይገኙበታል። (ደግሞ ኣበራ ሞላ ይዩ።)

በእጅ ጽሑፍና ማተሚያ ቤቶች ብቻ ይቀርብ የነበረው የግዕዝ ፊደል በ፲፱፻፹ ገደማ ኮምፕዩተራይዝድ ስለሆነ ኣጠቃቀሙ ወደ ኮምፕዩተር ዞሯል። ከእዚያም ወዲህ ፊደሉ የዩኒኮድ የዓለም ፊደላት መደብ ውስጥ ስለገባ እያንዳንዱ ቀለም የእራሱ ስፍራ ኣለው። (en:Ethiopic_(Unicode_block)) ይህ የኣማርኛ ውክፔድያ ድረገጽም የቀረበው በእዚሁ ፊደል ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህም ፊደሉን በእጅ ስልክ መጠቀም ተችሏል። ለፊደሉ ኣጠቃቀም ኣስፈላጊ ሆነው የተፈጠሩ ኣዳዲስ የቴክኖሎጂ ዘዴዎችም የዩናይትድ እስቴትስ የባለቤትነት መታወቂያ ወይንም ፓተንት ማግኘት ጀምረዋል። [1] Archived ሜይ 26, 2021 at the Wayback Machine [2]

ባህል እና ሃይማኖት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዋና መጣጥፍ፦ የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር

የህዝብ በዓላት
ቀን የበዓሉ ሥም የበዓሉ ሥም በእንግሊዝኛ አስተያየት
መስከረም ፩ እንቁጣጣሽ Ethiopian New Year  
መስከረም ፲፯ መስቀል Finding of the True Cross  
ጥቅምት ፳፬ ኢድ አል ፈጥር End of Ramadan ይለዋወጣል ፣ ይህ ቀን ለ ፲፱፻፺፰ ዓ. ም. ነው
ታኅሣሥ ፳፱ ገና Christmas  
ጥር ፪ ኢድ አል አደሃ Eid ul-Adha (Feast of the Sacrifice) ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ፲፱፻፺፰ ዓ. ም. ነው
ጥር ፲፩ ጥምቀት Epiphany  
የካቲት ፳፫ የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል Battle of Adowa Commemoration Day  
ሚያዚያ ፬ መውሊድ (የነብዩ መሃመድ የልደት ቀን) Birthday of The Prophet Muhammad ይለዋወጣል ፣ ይህ ቀን ለ ፲፱፻፺፰ ዓ. ም. ነው
ሚያዚያ ፲፫ ስቅለት Good Friday (Crucifixion) ይለዋወጣል ፣ ይህ ቀን ለ ፲፱፻፺፰ ዓ. ም. ነው
ሚያዚያ ፲፭ ትንሳዔ (ፋሲካ) Easter ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ ፲፱፻፺፰ ዓ. ም. ነው
ሚያዚያ ፳፯ የጀግኖች አርበኞች መታሰቢያ ቀን Patriots' Day  
ግንቦት ፳ ደርግ የወደቀበት ቀን End of the Derg Regime  

የውጭ መያያዣዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በ"Wikimedia Commons"
(የጋራ ፎቶዎች ምንጭ)
ስለ ኢትዮጵያ የሚገኛኙ
ተጨማሪ ፋይሎች አሉ።


ኢትዮጵያ

ታሪካዊ ቦታዎች - አክሱም | ላሊበላ | ጎንደር | ነጋሽ | ሐረር | ደብረ-ዳሞ | አዲስ አበባ
አስተዳደራዊ ክልሎች - ትግራይ | አፋር | አማራ | ኦሮሚያ | ሶማሌ | ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል | ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች | ጋምቤላ | ሐረሪ | አዲስ አበባ | ድሬዳዋ
ቋንቋዎች - አማርኛ | ግዕዝ | ኦሮምኛ | ትግርኛ | ጉራጊኛ | ሶማሊኛ | አፋርኛ | ሲዳምኛ | ሃዲያኛ | ከምባትኛ | ወላይትኛ | ጋሞኛ | ከፋኛ | ሃመርኛ | ስልጢኛ | ሀደሪኛ
መልክዓ-ምድር - አባይ | አዋሽ | ራስ-ዳሽን | ሶፍ-ዑመር | ጣና | ደንከል | ላንጋኖ | አቢያታ | ሻላ
ከተሞች - የኢትዮጵያ ከተሞች