መቀሌ
ከውክፔዲያ
| መቐለ | |
| መቐለ | |
| ከፍታ | 2,084 ሜ. |
| ኗሪ ስም | መቐለ |
| ሌላ ስም | መቀሌ |
| አገር | ኢትዮጵያ |
| የሕዝብ ቁጥር | 169,207 |
መቐለ (አማርኛ፦ መቀሌ) የትግራይ ክልል ዋና ከተማ ናት። ከአዲስ አበባ 783 ኪ.ሜ. ወደ ሰሜን ትገኛለች። ከ150,000 አስከ 250,000 የሚገመት የሕዝብ ብዛት ስላላት ከሰሜን ኢትዮጵያ ትልቁ ከተማ ያደርጋታል። መቐለ ለዮሐንስ ፬ኛ ዋና ከተማ በመሆን በ19ኛው ክፈለ ዘመን ነው የተመሠረተችው። መቐለ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ከተሞች በ ንግድና ትምህርታዊ ማዕከላዊነትዋ ትታወቃለች። እጅግ ታላቅና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ በታላቁ አፍሪካዊ ጄነራል ራስ አሉላ አባነጋ የተሰየመ አየረ ማረፊያ አላት። በተጨማሪም እንደነ መስፍን ኢንዱስትርያል፣ መሰቦ ሲሚንቶ፤ታላላቅ ፋብሪካዎችና ዩኒቨርሲቲ መቐለም በከተማዋ ይገኛሉ።
| ጅምር! (ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። እርስዎ ሊያስፋፉት ይችላሉ!) |
|
||||||||||||||||||||||||||||||||||||||
