ወልደያ
| ወልደያ | |
| ወልደያ ከተማ | |
| ከፍታ | 2112 ሜትር |
| ሌላ ስም | ወልዲያ |
| አገር | ኢትዮጵያ |
| ክፍለ ሐገር | ወሎ (አንጎት) |
| የሕዝብ ቁጥር | 42,710 |
ወልደያ ወይንም ወልዲያ ከደሴ ሰሜን 75 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ከላሊበላ ደግሞ በደቡብ ምስራቅ ያለ በኢትዮጵያ የአማራ ክልል ከተማ ሲሆን በሰሜን ወሎና በወልዲያ ወረዳ ይገኛል። ከኢኮኖሚ አንጻር ለሕንጻ ስራ የሚያገለግል የኖራ ምርት በአካባቢው በትንሹ መካሄዱ በታሪክ ይጠቀሳል[1]።
[ለማስተካከል] ታሪክ
ከተማው በታሪካዊ ቦታወች የተከበበ ሲሆን በ1834ዓ.ም. ወልደያን ጎብኝቶ የነበረው ሚስዮኑ ጆዓን ሉዊግ ክራፍ ደጅአዝማች ፋሪስ አሊጋዝ እና ወንድሙ ብሩ አሊጋዝ መምሪያቸውን በዚሁ ቦታ አድርገው እንደነበር ዘግቦት ይግኛል። ሁለቱ ወንድማማቾች በዚህ ወቅት ወረ ይመኑን ለመውጋት ተንቀሳቅሰው እንደነበር ይገልጻል[2]።
በ1880ዎቹ ወልደያ ለዝሆን አደን ተስማሚ ስለነበር በታሪክ ተጠቃሽነት አለው። ከ1880ዎቹ እስከ 1950ዎቹ ወልደያ የየጁ አውራጃ ማዕከል ነበር[1]። በዚህ ወቅት፣ የወልደያ ሆስፒታል በ1929 ዓ.ም በኮንተራክተሩ M.C.M. Pollera ተገነባ። ሆኖም ከመሬት መቀማት ጋር በተነሳ የቀዳማዊ ወያኒ አመጽ ተብሎ በሚታወቀው የ1940 አመጽ ከተማው ላይ በየጁወች ጥቃት ሲደረስ፣ እስር ቤቱ ተከፍቶ እሰረኞች ተለቀቁ። ሆኖም አመጹ የተሳካ አልነበረም [3] አለም አቀፍ ሃብታም በመሆኑ የሚታወቀው መሀመድ አላሙዲ በ1950ወቹ ለ10 አመት በወልደያ እንዳደገ ይጠቀሳል። ጥቅምት 8-9፣ 1980 ከተማዋ በደርግ አውሮፕላን ብትደበደብም የሞተ ሰው ግን አልተዘገበም።[4]
ከዚህ በተረፈ ወልደያ ላይ የሚገኙት አኖማ ማርያም (በዛፎች ተሸሽጎ ዋሻ ውስጥ የተደበቀ ቤ/ክርስቲያን[5]) እና ወልደያ ገብርኤል ለአካባቢው ታዋቂነትን ይሰጣሉ። ገነተ ማርያምም ከወልደያ ብዙ ሳይርቅ ይገኛል።
[ለማስተካከል] የሕዝብ ስብጥር
በ1998 ማዕከላዊ የስታትስቲክስ ባለስልጣን እንደተመነው የ42,710 ሰው መኖሪያ ሲሆን ከነሱም 22,216 ወንዶችና 20494 ሴቶች ይገኙበታል።[6]
| ዓ.ም.** | የሕዝብ ብዛት | የተማሪዎች ብዛት |
|---|---|---|
| 1959 |
8,505
|
|
| 1976 |
15,700
|
|
| 1984 |
24,500
|
|
| 1993 |
30,200
|
|
| 1998 |
42,700
|
[ለማስተካከል] ምንጮች
- ^ ሀ ለ "Local History in Ethiopia") The Nordic Africa Institute website (accessed 19 November 2007)
- ^ Journals of the Rev. Messrs. Isenberg and Krapf, Missionaries of the Church Missionary Society, Detailing their proceedings in the kingdom of Shoa, and journeys in other parts of Abyssinia, in the years 1839, 1840, 1841 and 1842, (London, 1843), p. 443
- ^ Bahru Zewde (2001). A History of Modern Ethiopia (second ed.). Oxford: James Currey. ISBN 0-85255-786-8.
- ^ Africa Watch Report, Ethiopia: "Mengistu has Decided to Burn Us like Wood": Bombing of Civilians and Civilian Targets by the Air Force, 24 July 1990
- ^ David Buxton, 1944
- ^ ማዕከላዊ የስታትስቲክስ ባለስልጣን, population.pdf
- ^ http://www.nai.uu.se/library/resources/dossiers/local_history_of_ethiopia/vw/ORTWEL.pdf
|
||||||||||||||||||||||||||||||||||||||
