አዋሳ
ከውክፔዲያ
አዋሳ ከአዋሳ ሃይቅ በታላቁ ሪፍት ቫሌ/ስምጥ ሸለቆ ላይ የሚገኝ ከተማ ነው። የደቡብ ሕዝቦች ክልል ዋና ከተማ ስተሆን በሲዳማ ዞን ተገኛለች። የአዲስ አበባ-ናይሮቢ መንገድ ላይ በላቲቱደና ሎንጁቱድ 7°3′ ሰሜን ኬክሮስ እና 38°28′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ናት። አዋሳ በውበትዋና በትልቅነትዋ ባሁኑ ጊዜ ታላቅ የቱሪስት መስህብ ያላት ነች።
በማዕከአዊ ስታቲስቲክ ባለስልጣን ትመና የ119,623 ሰው መኖሪያ ስትሆን ከነሱም 60,378 ወንዶች 59,245 ሴቶች ሆነው ተተምነዋል። አዋሳ የቀድሞ ሲዳሞ ክፍለ ሓገር ዋና ከተማ የነበረች የደቡብ ዩኒቨርሲቲ፥ የአንድ ኤርፖርትና የሰፊ ገበያ ማዕከል ናት። አዋሳ ከ1998 ዓ.ም. ጀምሮ ሃዋሳ በመባል የታወቃል። ይህን ተመርክዞ የደቡብ ዩኒቨርሲቲ ሃዋሳ በመባል ስሙ ተቀይሮአል።
| ጅምር! (ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። እርስዎ ሊያስፋፉት ይችላሉ!) |
|
||||||||||||||||||||||||||||||||||||||
