ጋምቤላ (ከተማ)

ከውክፔዲያ

ጋምቤላ በምዕራብ ኢትዮጵያ የምትገኝ ከተማ ስትሆን የጋምቤላ ክልል ዋና ከተማ ናት። በላቲቱድና በሎንጂቱድ 8°15′ ሰሜን ኬክሮስ እና 34°35′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ትገኛለች።

በ1998 የማዕከላዊ የስታትስቲክ ትመና መሰረት የ31,282 ሰዎች መኖሪያ ስትሆን ከነሱም መሃከል 16,163 ወንዶችና 15,119 ሴቶች ይገኙባታል። ጋምቤላ የአኙአክ እና የኑር ጎሳዎች መኖሪያ ስትሆን የየራሳቸው ገበያ በጋምቤላ ውስጥ አላችው። ከተማዋ የአንድ ኤርፖርት ባለቤትና የጋምቤላ ብሄራዊ ፓርክ ተጓዳኝ ናት።

ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ጋምቤላ የተመሰረተችብት ምክኒያት በባሮ ወንዝ ላይ ባላት አቀማመጥ ነው። ይህ ወንዝ በጊዜ ኢትዮጵያና እንግሊዝ ቡና ወዘተ. ወደ ሱዳንና ወደ ግብጽ ለመላክ ምቹ መንገድ መሆኑን ሁለቱም በማመናችው ነው። በ1902 እ.ኤ.አ. አጼ ምኒልክ ለእንግሊዝ ባሮ ወንዝ ላው አንድ ወደብ እንዲጠቀም ይፈቅዱና በ1907 እ.ኤ.አ. በስራ ላይ ከቀረጥ ቢሮ ጭምር ይውላል። በሱዳን የምድር ባቡር ኩባንያ የሚተዳደር የመርክብ አገልግሎት 1,366 ኪሎ ሜትር በመጓዝ ጋምቤላን ከካርቱም ጋር ያገናኛታል።

ሪቻርድ ፓንክርስት ዝገባ መሰረት በክረምት በወር ሁለት ጊዜ መርከቦች ሲመላለሱ ወንዙን ሲወርዱ 7 ቀናት፣ ሲወጡ ደግሞ 11 ቀናት ይፈጅባቸው ነበር።

ጋምቤላ በጣሊያን የምሰራቅ አፍሪካ ግዛት በ1936 እ.ኤ.አ. ተጠቃላ፥ በ1941 እ.ኤ.አ. በአንድ ከባድ ውጊያ በኋላ ወደ እንግሊዝ አስተዳደርነት ትዘዋውራ ነበር። ሱዳን ነጻ በወጣችበት በ1948 ዓ.ም. ለኢትዮጵያ ተመለሰች። በባሮ ላይ ያለው ወደብ በደርግ ጊዜ እንደተዘጋ ሆኖ፥ ይከፈት ይሆናል የሚል ተስፋ አለ።

በሦስት ዞኖችና በአንድ ልዩ ወረዳ ሥር በሚገኙ 13 ወረዳዎች፣ በ241 ቀበሌዎችና በአንድ የከተማ አስተዳደር የተዋቀረችው ጋምቤላ ጠቅላላ የቆዳ ስፋቷ 30,065 ካሬ ኪሎ ሜትር ነው፡፡ ሃያ በመቶው የክልሉ መሬት በደን የተሸፈነ ነው፡፡ ጋምቤላ በሰሜንና በምሥራቅ ከኦሮሚያ ክልል ጋር ስትዋሰን፣ በደቡብ ምዕራብ ከአዲሲቱ ደቡብ ሱዳን ጋር በሰፊው ትዋሰናለች፡፡ ከአዲስ አበባ በ776 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው የጋምቤላ ከተማ በቅርቡ 100ኛ ዓመት የልደት በዓሏን ያከበረች ሲሆን፣ እንደ ብዙዎቹ የአገሪቱ ዕድሜ ጠገብ ከተሞች ዘርፈ ብዙ ችግሮችን የምትጋፈጥ የበረሃ ገነት ነች፡፡ ከ60 ሺሕ በላይ ነዋሪዎች ያላት ጋምቤላ በአብዛኛው የሚኖሩባት

እንግሊዞች በቅኝ ግዛት ዘመን ሱዳንን በሚያስተዳድሩበት ወቅት ለወታደራዊም ሆነ ለንግድ እንቅስቃሴው መናኸሪያ በማድረግ ሲጠቀሙባት እንደነበር በታሪክ የሚነገርላት ጋምቤላ፣ ከ19ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ጀምሮ የኢትዮጵያ አካል እንደነበረችና በኋላም ሱዳን እ.ኤ.አ በ1956 ነፃነቷን ስትቀዳጅ በኢትዮጵያ የአስተዳደር ክልል ሙሉ ለሙሉ መካተቷም በታሪክ ድርሳናት ተወስቷል፡፡ በክልሉ አምስት ብሔረሰቦች ይኖራሉ፡፡ ጋምቤላ በእነዚህ ብሔረሰቦች የእርስ በርስ ግጭትና በአካባቢው ድንበርተኛ በሆነችው ሱዳን ለረዥም ዓመታት በቆየው የእርስ በርስ ጦርነት ስትታመስ መኖሯም ይታወቃል፡፡

ዚህም ከአገሪቱ ታላላቅ ተፋሰሶች አንዱ በሆነው የባሮ ወንዝ ላይ ረዥም የተባለውን ድልድይ በመገንባት የአካባቢውን ሁኔታ ሲያረጋጋ፣ ለፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማርያምም ለየት ያለ አድናቆትንና ፍቅርን ያስገኘላቸው አጋጣሚ እንደነበርም በአካባቢው ነዋሪዎች በስፋት ይወሳል፡፡ አሁንም ድረስ በከተማዋ ጋምቤላ አቋርጦ የሚያልፈው ባሮ ወንዝ ላይ በተገነባው ድልድይ በአንድ በኩል ብቻ በርከት ያለ ሕዝብ ሲጓጓዝ የተመለከተ ጎብኚ ምክንያቱ ምን እንደሆነ ሲጠይቅ፣ ከነዋሪዎች ‹‹ኮሎኔሌ መንግሥቱ የተራመዱበት ጥግ ስለሆነ ነው›› የሚል ምላሽ ሊያገኝ ይችላል፡፡

በእርግጥ በተደጋጋሚ ጊዜ እንደሚደመጠው የቀድሞው መሪ በባሮ ወንዝ ላይ ባስገነቡት ድልድይ የአካባቢው ነዋሪዎች የእርስ በርስ ግንኙነታቸውን ከማጠናከር ባለፈ፣ በኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ተጠቃሚ በመሆናቸው እሳቸው ጥለው ያለፉት ከፍተኛ ቅርስ መሆኑን ይመሰክራሉ፡፡ በአንፃሩ የከተማው የትራፊክ አስተናባሪዎች እግረኞች ብቻ ሳይሆኑ ተሽከርካሪዎችም ጭምር በተራ የሚተላለፉት የድልድዩን ደኅንነት ለመጠበቅ ታስቦ እንደሆነ በመግለጽ የመጀመሪያውን አስተያየት ያጣጥሉታል፡፡ ‹‹መንግሥቱ የባሮን ድልድይ በማሠራቱ ዘለዓለማዊ ፍቅርን በእኛ ዘንድ አኑሯል፤›› ያሉት የዕድሜ ባለፀጋው አኩሉ ኦጆን፣ ምናልባትም ፕሬዚዳንቱ በቆዳ ቀለማቸው ለጋምቤላ ሕዝቦች ቅርብ ከመሆናቸው ጋር በተያያዘ ትክክለኛ የአገር መሪ እንደነበሩም በማወደስ ጭምር ፈገግታ የተሞላበት አስተያየታቸውን ይሰጣሉ፡፡

የቀድሞው መሪ በጋምቤላ የባሮ ወንዝ ድልድይን ብቻ ሳይሆን የጋምቤላ አውሮፕላን ማረፊያን ያስገነቡ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ በአካባቢው ሕዝብ የተለየ ቦታ እንዳላቸው ቢነገርም፣

ጋምቤላ ከመጀመሪያው ጀምሮ በሕወሃት አስተዳደር ክፉኛ ተጎድታለች፤ በመሬቷ ልማትና በከርሰ ምድር ሃብቷ ምክንያት በዐባይ ጸሐዬና በዶ/ር ገብረአብ ባርናባስ የተመራ በ1994 የተጀመረው የዘር ማጥፋት አሁንም ሙሉ ለሙሉ ቆሟል ለማለት ያስቸግራል፣ በቅርቡ በመዥነገሮች ላይ የሕወሃት ወታደሮች የፈጸሙትን ጭፈጨፋ ስናስብ!

በክልሏ የተፈጥሮ ሃብት ላይም የተካሄደውና የሚካሄደው ጭፍጨፋ በሃገራችን በሁሉም መልኩ በሲቪል ማኅበረስብና የመንግሥቱን መዋቅር በሚቆጣጠረው የንዑስ ብሄረሰብ ወኪል የሆነው በጦር ኃይል የሚደገፈው ሕወሃት የሚፈጽመው የጥፋትና የጠላትነንት ሥራ ብዙ ማስረጃዎች እየቀረቡበት ነው።

የኢትዮጵያን ተተኪ የሌለው የተፈጥሮ ሃብት በብር 16.7 ሚሊዮን ክፍያ በባዕዳን በማስጨፍጨፍ፡ ሕወሃትና ጭፍሮቹን በሃገሪቱ ላይ ያላቸውን የጠላትነት ጥላቻ አረጋግጠዋል። ይህ ድርጊትም ባዕድ ቅኝ ገዥ ከሚያደርገው ተለይቶ የሚታይ አይደለም –

በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ ጉማሬ ቀበሌ ውስጥ ይገኛል፡፡ የጉማሬ ደን ከ1,800 እስከ 2,200 ሜትር ከፍታ ላይ ደልዳላ ቦታ ይዞ ከተራራው ወደታች ሲወርድ ቁልቁለታማ ሸለቆዎች በብዛት ያሉበት ነው፡፡ ከዚህ ተራራማና በጥቅጥቅ ተፈጥሯዊ ደን የተሸፈነ ምድር በርካታ ወንዞችና ወንዞችን የሚፈጥሩ ምንጮች ይነሳሉ፡፡ በአጠቃላይ 40 የሚደርሱ ምንጮችና ወንዞች ከአባቢው የሚነሱ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ሻይ፣ ጋጃ፣ ካጃዲ፣ ፋኒና ቢታሽ ተጠቃሾች ናቸው፡፡

ከአካባቢው የሚነሱ የውኃ ምንጮች በኢትዮጵያ ከሚገኙ 12 ተፋሰሶች አንዱ የሆነው የባሮ አኮቦ ተፋሰስ አካል ናቸው፡፡ የጋምቤላ ክልል እስትንፋስ የሆነው ባሮ አኮቦ ወንዝ የነጭ ዓባይ ትልቅ ገባር እንደሆነ ይታወቃል፡፡

በሌላ በኩል ለውኃ አካላቱ መሠረት የሆነው የአካባቢ ተፈጥሯዊ ደን በርካታ አገር በቀል ዛፎችን ያካተተ ነው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ቀረሮና ገተማ ዛፎች ተጠቃሽ ናቸው፡፡

የገተማ ዛፍ አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴን ጨምሮ በርካታ ኢንቨስተሮችና የአካባቢው ንብ አናቢዎች ማር እንዲያመርቱ ምክንያት የሆነ ነው፡፡ የገተማ ዛፍ የተለየ ጥራት ያለው የማር ምርት ማስገኘት የሚችል መሆኑን የአካባቢው ማኅበረሰብ ይተርክለታል፡፡

ከማር ምርት በተጨማሪ ተፈጥሯዊው የጉማሬ ደን በርካታ ቅመማ ቅመሞች የሚገኝበት መሆኑም ይነገርለታል፡፡ ነገር ግን የህንዱ ኩባንያ ቬርዳንታ ሐርቨስትስ ያለ በቂ ጥናት ቦታውን መረከቡ የአካባቢውን ብዝኃ ሕይወት እየጎዳ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ፡፡

የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በ1997 ዓ.ም. ተመሥርቶ በ1999 ዓ.ም. ነው ሥራ የጀመረው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በቤንች ማጂ ዞን በ52 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ቴፒ ከተማ ውስጥ ይገኛል፡፡